TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ሰበር ዜና‼️

አቶ #አወል_አርባ የአፋር ብሄራዊ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሆነው #ተሾሙ። የክልሉ ምክር ቤቱ 5ኛ ዙር 4ኛ ዓመት የስራ ዘመን 2ኛ አስቸኳይ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል።

በዚህም አቶ አወል አርባን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አድርጎ ሾሟል። አቶ አወል አርባ የአፋር ብሄራዊ ዴሞክራሲዊ ፓርቲ (አብዴፓ) ምክትል ሊቀ መንበር ሆነው በማገልገል ላይ ይገኛሉ።

ምክር ቤቱ በቀጣይም የምክር ቤቱን አፈ ጉባኤ በመምረጥ በርዕሰ መስተዳድሩ የሚቀርቡ የካቢኔ አባላትን ሹመት እንደሚያጸድቅ ይጠበቃል።

ከዚህ ባለፈም ምክር ቤቱ በሀገር አቀፍ ደረጃ እየተካሄደ ያለውን ለውጥ ውጤታማ፣ ቀልጣፋና ተቋማዊ በሆነ መልኩ ለመተግበር የሚያስችል የአስፈፃሚ አካላትን አደረጃጀት፣ ስልጣንና ተግባር እንደገና ለመወሰን በተዘጋጀ አዋጅ ላይም ውይይት ያደርጋል ተብሎም ነው የሚጠበቀው።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia