TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ማስታወቂያ📌ባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ⬇️

ቀን 05/13/2010 ዓ.ም

በ2010 ዓ/ም ሁለተኛው ወሰነ ትምህርት የ3ኛ ዓመት የቴክኖሎጅ ተቋም ተማሪዎች ዩኒቨርሲቲው ከ2003 ዓ.ም ጀምሮ እየተገበረ ባለው ስርዓተ ትምህርት መሰረት ‘Holistic‘ ፈተና አንፈተንም ማለታቸውን ተከትሎ በተፈጠረዉ አለመረጋጋት ጥፋተኛ በመባላቸው በቴክኖሎጅ ተቋም ሴኔት ለአንድ ዓመት ከትምህርት ገበታቸው እንዲታገዱ መወሰኑ ይታወቃል፡፡ ይሁን እንጅ ከተማሪ ወላጆች እና ከተማሪዎች ህብረት ጋር በተደረገ ተከታታይ ውይይት መሰረት ተማሪዎች በተማሪዎች ህብረት በኩል ባቀረቡት የይግባኝ አቤቱታ መነሻነት ዩኒቨርሲቲው የይግባኝ አቤቱታውን ተመልክቶ የሚከተሉትን ውሣኔዎች አስተላልፏል፡፡

1. ለአንድ ዓመት ከትምህርት ገበታ መታገድ የሚለው #ቅጣት በመጨረሻ የጽሑፍ ማስጠንቀቂያ #ተሻሽሎ ተማሪዎች ወደ መደበኛ ትምህርታቸው እንዲመለሱ፣

2. በ2010 ዓ/ም የ2ኛው ወሰነ ትምህርት ያልተፈተኑትን #ማጠቃለያ ፈተና ተቋሙ በሚያወጣው መርሃ ግብር መሠረት እንዲፈተኑ፣

3. በ2011 ዓ.ም የሚሰጠው ‘’Holistic‘’ ፈተና ተቋሙ ባፀደቀው ስርዓተ ትምህርት እና የአካዳሚክ ህግ መሠረት በሚወጣው የጊዜ ሰሌዳ እንዲፈተኑ፣

ስለሆነም የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ የ3ኛ ዓመት የቴክኖሎጅ ተቋም ተማሪዎች ይህን ውሣኔ አውቃችሁ ቅድመ ዝግጅት እንድታደርጉ እየገለጽን የመግቢያ ጊዜውን በጥሪ ማስታወቂያ የምናሳውቅ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

ባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ
@tsegabwolde @tikvahethiopia