TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ከሰጡት መግለጫ የነሷቸው ዋና ዋና ነጥቦች:-

• ኢትዮጵያ ውስጥ ሁሉም #አሸናፊ የሚሆንበት አውድ እንዲፈጠር እንፈልጋለን፡፡

• የአሸናፊዎች ስብስብ አሸናፊ አገር ይፈጥራል፡፡

• አንዱ አሸናፊ አንዱ #ተሸናፊ የሚሆንበት የፖለቲካ ስርዓት ኢትዮጵያ ውስጥ አያስፈልገንም ይበቃናል፡፡

• ባንድራ የሀሳብ መግለጫ፣ የፓርቲዎች አርማ ነው፤ መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚፈልገው ከሆነ ባንድራ በውይይት ሊቀየር ይችላል፣ በጉልበት ማስቀየር የሚፈልግ ካለ እሱ ጉልበት እንዳለው ሌለውን ጉልበት ስላለው አያዋጠም፡፡

• የትኛውም ጫፍ የፖለቲካ አመለካከት ያለው የፖለቲካ ኃይል ካለ የኢትዮጵያ ህዝብ መቀበል አለበት፣ የማግለል ፖለቲካ መቆም አለበት፡፡

• ወንድም ወንድሙን ገድሉ ማሸነፍ አይችልም፤ በሀሳብ ግን አሸናፊ መሆን ይቻላል፡፡

©etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia