TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ቤኒሻንጉል_ጉምዝ

ለኢንቨስትመንት መሬት ከወሰዱና ከአላለሙ ባለሃብቶች በመንጠቅ ለአልሚ ባለሀብቶችና ለወጣቶች እንደሚሰጥ የቤኒሻንጉል ክልል ምክር ቤት አስታወቀ፡፡

ምክር ቤቱ ከትናንት በስቲያ ማክሰኞ በጀመረው የ5ኛ 5 ዓመት 5ኛ የስራ ዘመን 9ኛ ጉባኤም የአስፈጻሚ አካላት ሪፖርት ሲገመግም እንደገለጸው፣ በተለይ የግብርናውንና የማዕድን ዘርፍ ስራዎችን ለመስራት መሬት ወስደው ያላለሙት ይነጠቃሉ፤ ለወጣቶችና ለአልሚ ባለሃብቶችም ይሰጣል፡፡

የቤኒሻንጉል ጉምዝ ክልል ምክር ቤት የሕዝብ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ተስፋዬ ታደሰ በተለይ ለአዲስ ዘመን እንደገለጹት፤ ክልሉ የበርካታ ጸጋዎች ባለቤት እንደሆነ ጠቅሰው፤ በተለያዩ ዘርፎች ማልማት የሚፈልጉ ባለሃብቶች መሬት ተረክበው መሰማራታቸውን ተናግረዋል፡፡

Via አዲስ ዘመን
@tsegabwolde @tikvahethiopia