TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
በሀዋሳ ከተማ አተት መከሰቱ ተሰማ!

በሀዋሳ ከተማ አጣዳፊ ትውከትና ተቅማጥ/አተት መከሰቱን የሃዋሳ ከተማ ጤና መምሪያ አስታወቀ። በሽታው የታየው በጥልቴ ቀበሌ ሲሆን በበሽታዉ የተጠቁ 2 ግለሰቦች የህክምና አግልግሎት እያገኙ መሆኑን የገለፁት የሐዋሳ ከተማ ጤና መምሪያ ሃላፊ አቶ #ቡሪሶ_ቡላሾ በሽታውን ወደ ሌሎች የከተማው ክፍሎች ሳይዛመት ከወዲሁ ለመግታት ሁሉም የህብረተሰቡ ክፍል መረባረብ እንዳለበት አሳስበዋል። በሽታው ቶሎ ካልተገታ ከከተማው አልፎ ወደ ሲዳማ ዞን ሊዛመት እንደሚችል የጠቆሙት ሀላፊው ይህ እንዳይሆን ለማድረግ ከዘርፉ ባለሙያወች እና ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ በወንዶ ገነት ከተማ ውይይት እየተደረገ ይገኛል።

Via #SMN
@tsegabwolde @tikvahethiopia