TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አብዱል በቁጥጥር ስር ዋለ‼️

ባለፉት ወራት በቤኒሻንጉል ክልል እየተንቀሳቀሰ ማሕበራዊ ሰላም #ሲያደፈርስ የነበረውና ከጸረ ሰላም ሃይሎች ጋር ተቀናጅቶ በርካታ ወንጀሎችን በመፈጸም የተጠረጠረው ግለሰብ ከትላንት በስቲያ #በፌደራል_ፖሊስ ቁጥጥር ስር መዋሉን ጉለሌ ፖስት ከምጮቼ ሠማሁ ብሎ ዘግቧል።

#አብዱል_ወሃብ የተባለውና የቤኒሻንጉል ነፃ አውጪ ግንባር ሊቀ መንበር የነበረው ይህ ግለሰብ ቀደም ሲል በኤርትራ ይንቀሳቀስ የነበረውን ግንባር ሲመራ ቢቆይም፤ በአገሪቱ በተፈጠረው ለውጥ ወደክልሉ ከተመለሰ በኋላ ለውጡን ለመቀልበስ ከሚፈልጉ ሃይሎች ጋር
በመቀናጀት በበርካታ ወንጀሎች ሲፈለግ መቆየቱን የጉለሌ ፖስት ምንጮች ጠቁመዋል።

አብዱል ወሃብ በትናንትናው ዕለት በቁጥጥር ስር ከመዋሉ በፊት በፌደራልፖሊስ አባላቱ ላይ ተኩስ ከፍቶ ለማምለጥ ጥረት ያደረገ ሲሆን በተደረገው የተኩስ ልውውጥ ተመቶ በቁጥጥር ስር ውሏል ተብሏል።

እንደጉለሌ ፖስት ምንጮች ገለጻ ተጠርጣሪው #ለማምለጥ ባደረገው ጥረት የክልሉ ልዩ ሃይል የተወሰኑ አባላት ስልታዊ ድጋፍ ሲያደርጉለት እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ...

በያዝነው ዓመት መጀመርያ ላይ በሕዝቡ ላይ የሚደርሰውን እንግልት ለመከላከል ቄሮዎችን አደራጅታችኋል በሚል በቤኒሻንጉል ክልል እስር ቤት የሚገኙት ዘጠኝ አዛውንቶች እስካሁን ፍርድ ቤት ያለመቅረባቸውን የመረጃ ምንጮቼ ገልጸዋል ሲል ጉለሌ ፖስት ዘግቧል። በተለይ ኦቦ #ተስፋዬ_አመኑ እና ኦቦ #መላኩ_ቀጄላ የተባሉት አዛውንቶች በሕመም ላይ የሚገኙ መሆኑ በጣም አሳሳቢ እንደሆነባቸውና መንግስት አስቸኳይ እልባት እንዲሰጣቸው እኒሁ ወገኖች ጥሪ አቅርበዋል።

ምንጭ፦ ጉለሌ ፖስት
@tsegabwolde @tikvahethiopia