TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#Amhara

" የተከሰተው ችግር #በውይይት_ተፈቷል ፤... የሰላም #ስምምነትም ተደርጓል " - የሰ/ ወሎ ዞን አስተዳደር

የሰሜን ወሎ ዞን አስተዳደር ፤ ከሰሞኑን ከክልል ልዩ ሀይል መልሶ ማደራጀት ጋር ተያይዞ ተከስቶ የነበረው የፀጥታ ችግር በውይይት መፈታቱን ዛሬ ምሽት አሳውቋል።

የፀጥታ ችግሩን ለመፍታት በሐይማኖት አባቶች፣ በአገር ሽማግሌዎችና በዘወልድ ሽምግልና ስርዓት የሠላም ስምምነት ተደረጓል ብሏል።

በሰላም ስምምነት ስነስርዓቱ ላይ ፦
- የአገር መከላከያ ሠራዊት ፣
- የክልል ፣ የዞን ፣ አመራሮች
- የምስራቅ አማራ ፋኖ አመራሮች
- የአገር ሽማግሌዎች የሰላም ስምምነቱን አስመልክተው መግለጫ መስጠታቸውንም የዞን አስተዳደሩ አመልክቷል።

ስምምነቱን በተመለከተ የሰ/ወሎ ዞን አስተዳደር ለህዝብ ያሰራጨው መረጃ #ከላይ ተያይዟል።

NB. ውድ ቤተሰቦቻችን በዚህ የሰ/ወሎ ዞን አስተዳደር መግለጫ ዙሪያና ስምምነቱ ዙሪያ ከፋኖ አደረጃጀት አመራሮች ዘንድ የሚሰጥ አስተያየት ካለ ተከታትለን የምናሳውቅ ይሆናል።

@tikvahethiopia
👎2.24K👍1.91K193🕊182🙏57😢24😱23🥰20