TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አቶ ኢሳያስ በዋስ እንዲወጡ ተወሰነ‼️

ፍርድ ቤቱ መርማሪ ፖሊስ አቶ #ኢሳያስ_ዳኘው በዋስ ሊለቀቁ አይገባም በሚል ያቀረበውን ይግባኝ ውድቅ አደረገ። በከባድ የሙስና ወንጀል የተጠረጠሩት አቶ ኢሳያስ ዳኘው በተጠረጠሩበት ወንጀል በፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 10ኛ የወንጀል ችሎት ቀርበው ጉዳያቸውን ሲከታተሉ ከቆዩ በኋላ በ50 ሺህ ብር ዋስ እንዲወጡ #ተፈቅዶላቸዋል

መርማሪ ፖሊስም ግለሰቡ በዋስ መውጣት የለባቸውም በሚል ለጠቅላይ ፍርድ ቤት ያቀረበው ይግባኝ ውድቅ ተደርጎበታል።

በመሆኑም ከዚህ ቀደም በተወሰነው መሰረት በ50 ሺህ ከሃገር እንዳይወጡ በተጣለ እገዳ #በዋስ እንዲለቀቁ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ውሳኔውን አፅንቷል።

አቶ ኢሳያስ ዳኘው በኢትዮ ቴሌኮም የኤን ጂ ፒ ኦ ዳይሬክተር ሆነው በሚሰሩበት ወቅት ለሜቴክ የተሰጠን ውል በማሻሻልና ክፍያ እንዲፈጸም በማድረግ በመንግስት ላይ ጉዳት እንዲደርስ አድርገዋል በሚል በከባድ የሙስና ወንጀል ነበር የተጠረጠሩት።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia