ከአምቦ ዩኒቨርሲቲው መምህር ስዩም ተሹመ የተገኘ መረጃ...
ዶ/ር አብይ አህመድ እና ፕ/ት #ኢሳያስ_አፈወርቂ #በአቡ_ዲያቢ ተገናኝተው ተወያይተዋል።
================================
ከአንድ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባልደረባ ባገኘሁት መረጃ መሰረት፣ የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ትላንት የአልጄርሱን ስምምነት ለመቀበል ያሳለፈው ውሳኔ የኢትዮጲያ መንግስት በተናጠል የወሰደው እርምጃ አለመሆኑን ለመረዳት ችያለሁ። ከዚያ ይልቅ፣ የኢትዮጲያ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከኤርትራው ፕረዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በአቡ ዲያቢ ተገናኝተው ተወያይተዋል።
ጠ/ሚ አብይ በሳውዲ አረቢያ ያደረጉትን ጉብኝት ካጠናቀቁ በኋላ ወደ አቡ-ዲያቢ ተጉዘው እንደነበር ይታወሳል። በተመሳሳይ ወቅት የኤርትራው ፕረዜዳንት “ለሕክምና” በሚል ሰበብ ወደ አቡ-ዲያቢ ማቅናታቸው ይታወሳል። ከላይ የጠቀስኩት የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባልደረባ እንደነገረኝ ከሆነ ሁለቱ መሪዎች በአቡ-ዲያቢ ተገናኝተው መክረዋል።
በመሆኑም የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የአልጄርሱን ስምምነት ለመቀበል የወሰነው በተናጠል ሳይሆን በቅድሚያ ከኤርትራ መንግስት ጋር በመነጋገር የተወሰደ እርምጃ ነው።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ዶ/ር አብይ አህመድ እና ፕ/ት #ኢሳያስ_አፈወርቂ #በአቡ_ዲያቢ ተገናኝተው ተወያይተዋል።
================================
ከአንድ የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባልደረባ ባገኘሁት መረጃ መሰረት፣ የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ ትላንት የአልጄርሱን ስምምነት ለመቀበል ያሳለፈው ውሳኔ የኢትዮጲያ መንግስት በተናጠል የወሰደው እርምጃ አለመሆኑን ለመረዳት ችያለሁ። ከዚያ ይልቅ፣ የኢትዮጲያ ጠ/ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ ከኤርትራው ፕረዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ጋር በአቡ ዲያቢ ተገናኝተው ተወያይተዋል።
ጠ/ሚ አብይ በሳውዲ አረቢያ ያደረጉትን ጉብኝት ካጠናቀቁ በኋላ ወደ አቡ-ዲያቢ ተጉዘው እንደነበር ይታወሳል። በተመሳሳይ ወቅት የኤርትራው ፕረዜዳንት “ለሕክምና” በሚል ሰበብ ወደ አቡ-ዲያቢ ማቅናታቸው ይታወሳል። ከላይ የጠቀስኩት የውጪ ጉዳይ መስሪያ ቤት ባልደረባ እንደነገረኝ ከሆነ ሁለቱ መሪዎች በአቡ-ዲያቢ ተገናኝተው መክረዋል።
በመሆኑም የኢህአዴግ ሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ የአልጄርሱን ስምምነት ለመቀበል የወሰነው በተናጠል ሳይሆን በቅድሚያ ከኤርትራ መንግስት ጋር በመነጋገር የተወሰደ እርምጃ ነው።
@tsegabwolde @tikvahethiopia