TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሳዛኝ ዜና‼️

በሰሜን ወሎ ዞን ላሊበላ ከተማ በአንድ ግለሰብ #በተተኮስ ጥይት የ8 ሰዎች ህይወት አለፈ፡፡ በላሊበላ ከተማ ቀበሌ 01 ዛሬ ጠዋት በሁለት ሰዎች መካከል በተከሰተ ግጭት ጉዳዩን #ለማረጋጋት በሞከሩ ሰዎች ላይ ግለሰቡ ጥይት ተኩሷል፤ ይላል የፖሊስ መረጃ፡፡
በተተኮሰው ጥይትም የ8 ሰዎች ህይወት አልፏል፤ 6 ሰዎች ደግሞ ቆስለዋል፡፡

የቆሰሉት ሰዎች አሁን ሆስፒታል ገብተው የህክምና እርዳታ እየተደረገላቸው መሆኑን የአማራ ክልል ፖሊስ ኮሚሽን የሚዲያ አስተባበሪ ምክትል ኮማንደር መሠረት ላቀ ለአማራ ብዙኃን መገናኛ ድርጅት አስታውቀዋል፡፡ ምክትል ኮማንደሩ እንደገለጹልን ወንጀሉን የፈጸመው ግለሰብ በፖሊስ ተይዞ ምርመራ እየተደረገበት ነው፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia