TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ኢትዮጵያ እና አሜሪካ ወታደራዊ ልምምድ ሊያደርጉ ነው። ወታደራዊ ልምምዱ የአሜሪካ መከላከያ አባላት ከኢትዮጵያ መከላከያ ሃይል ጋር በጥምረት የሚካሄድ መሆኑ ተገልጿል። ልምምዱ #በሶማሊያ በተሰማራው የአፍሪካ ህብረት ሰላም አስከባሪ ሃይል (አሚሶም) አባላትን አቅም ማሳደግ ላይ ያተኮረ ሲሆን፥ ወደ 1 ሺህ 100 የሚጠጉ ወታደራዊና የመንግስት ሃላፊዎች ይሳተፉበታል። ልምምዱ የመከላከያ አባላትን ዝግጁነትና አቅም በማሳደግ ሰላምን ለማስከበር የሚደረገውን ጥረት እንዲደግፉና በቀጠናው ሰላምን ለማስፈን እንደሚያግዝም ታምኖበታል። የፊታችን ሰኞ የሚጀመረው የ2019 ወታደራዊ ልምምድ ለ17 ቀናት እንደሚቆይ በኢትዮጵያ ከአሜሪካ ኤምባሲን ጠቅሶ ኤፍ ቢሲ ዘቧል።

በወታደራዊ ልምምዱ ላይ፦

•ከብራዚል
•ከብሩንዲ
•ከካናዳ
•ከጂቡቲ
•ከፈረንሳይ
•ከጀርመን
•ከጣሊያን
•ከኬንያ
•ከኔዘርላንድስ
•ከሩዋንዳ
•ከሶማሊያ
•ከኡጋንዳ እና ዩናይትድ ኪንግደም የተውጣጡ #ወታደሮች ይሳተፋሉ።

Via #EPA/fbc/
🗞ቀን ሃምሌ 3/2011 ዓ/ም
@tsegabwolde @tikvahethiopia