የተማሪዎች ግጭት በወልደያ ዩኒቨርስቲ...
ትናንት ረቡዕ ሌሊት በወልደያ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች መካከል በተነሳ ግጭት ከ10 በላይ ተማሪዎች መጎዳታቸው ተሰማ። በድንጋይ እና በዱላ በተደረገው ድብድብ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት አንድ ተማሪ ለከፍተኛ ህክምና መላኩ ተገልጿል።
የዩኒቨርሲቲው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ተፈራ አስናቀ በተለይ ለዶይቼ ቬለ DW እንደገለፁት፤ በግጭቱ ተማሪዎች ላይ ከደረሰው ጉዳት በተጨማሪ የመኝታ ክፍሎቻቸው #መስኮት እና #በሮችም ተሰባብረዋል። የፀቡ መነሻ ከሰሞኑ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተፈጠሩ ግጭቶች ጋር ሳይገናኝ እንዳልቀረም አመልክተዋል።
በተመሳሳይ ከሰሞኑን በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረው ግጭት ትምህርት የተቋረጠ ሲሆን ዛሬም ትምህርት እንዳልተጀመረ እና ተማሪዎችም ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር እየተወያዩ እንደሆነ ታውቋል። ሰሞኑን በደብረ ማርቆስ እና አክሱም ዩኒቨርሲቲዎች በተማሪዎች መካከል በተፈጠሩ ግጭቶች የሁለት ተማሪዎች ሕይወት ማለፉ አይዘነጋም።
Via #DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ትናንት ረቡዕ ሌሊት በወልደያ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች መካከል በተነሳ ግጭት ከ10 በላይ ተማሪዎች መጎዳታቸው ተሰማ። በድንጋይ እና በዱላ በተደረገው ድብድብ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት አንድ ተማሪ ለከፍተኛ ህክምና መላኩ ተገልጿል።
የዩኒቨርሲቲው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ተፈራ አስናቀ በተለይ ለዶይቼ ቬለ DW እንደገለፁት፤ በግጭቱ ተማሪዎች ላይ ከደረሰው ጉዳት በተጨማሪ የመኝታ ክፍሎቻቸው #መስኮት እና #በሮችም ተሰባብረዋል። የፀቡ መነሻ ከሰሞኑ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተፈጠሩ ግጭቶች ጋር ሳይገናኝ እንዳልቀረም አመልክተዋል።
በተመሳሳይ ከሰሞኑን በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረው ግጭት ትምህርት የተቋረጠ ሲሆን ዛሬም ትምህርት እንዳልተጀመረ እና ተማሪዎችም ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር እየተወያዩ እንደሆነ ታውቋል። ሰሞኑን በደብረ ማርቆስ እና አክሱም ዩኒቨርሲቲዎች በተማሪዎች መካከል በተፈጠሩ ግጭቶች የሁለት ተማሪዎች ሕይወት ማለፉ አይዘነጋም።
Via #DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia