TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የተማሪዎች ግጭት በወልደያ ዩኒቨርስቲ...

ትናንት ረቡዕ ሌሊት በወልደያ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች መካከል በተነሳ ግጭት ከ10 በላይ ተማሪዎች መጎዳታቸው ተሰማ። በድንጋይ እና በዱላ በተደረገው ድብድብ ከፍተኛ ጉዳት የደረሰበት አንድ ተማሪ ለከፍተኛ ህክምና መላኩ ተገልጿል።

የዩኒቨርሲቲው የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ተፈራ አስናቀ በተለይ ለዶይቼ ቬለ DW እንደገለፁት፤ በግጭቱ ተማሪዎች ላይ ከደረሰው ጉዳት በተጨማሪ የመኝታ ክፍሎቻቸው #መስኮት እና #በሮችም ተሰባብረዋል። የፀቡ መነሻ ከሰሞኑ በተለያዩ ዩኒቨርሲቲዎች ከተፈጠሩ ግጭቶች ጋር ሳይገናኝ እንዳልቀረም አመልክተዋል።

በተመሳሳይ ከሰሞኑን በደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ በተፈጠረው ግጭት ትምህርት የተቋረጠ ሲሆን ዛሬም ትምህርት እንዳልተጀመረ እና ተማሪዎችም ከመንግሥት ባለሥልጣናት ጋር እየተወያዩ እንደሆነ ታውቋል። ሰሞኑን በደብረ ማርቆስ እና አክሱም ዩኒቨርሲቲዎች በተማሪዎች መካከል በተፈጠሩ ግጭቶች የሁለት ተማሪዎች ሕይወት ማለፉ አይዘነጋም።

Via #DW
@tsegabwolde @tikvahethiopia