የ2011 የህዳሴግድብ የቦንድ ሽያጭ በአንድ ቢሊዮን ብር ማሽቆልቆሉ ተሰማ!
የታላቁ ህዳሴ ግድብ የግንባታ ወጪን ለመሸፈን ታስቦ ለህዝብ ሲቀርብ የነበረው የቦንድ ሽያጭ በ2010 ከነበረበት 2.14 ቢሊዮን ብር ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በማሽቆልቆል በተገባደደው የ2011 በጀት ዓመት 970 ሚሊዮን ብር ብቻ ሆኖ ተመዘገበ።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ብሔራዊ አስተባባሪ ጽሕፈት ቤት የሚዲያ ግንኙነት ኀላፊ ኃይሉ አብርሃም ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ እንደገለፁት፣ በግድቡ መዘግየት እና ተያያዥ ችግሮች ምክንያት ህብረተሰቡ አመኔታ ማጣቱን እንደ ምክንያት ገልፀው ይህም የቦንዱን ሽያጭ አቀዛቅዞታል ብለዋል።
‹‹የህዳሴው ግድብ ግንባታ #ቆመ የሚል አመለካከት በመፈጠሩ ምክንያት ሀብት ከማሰባሰብ ይልቅ ማህበረሰቡ ጋር ያለውን የመረጃ ብዥታ ማጥራት ላይ ትኩረት አድርገን ስንሠራ ቆይተናል›› ሲሉም ተናግረዋል።
https://telegra.ph/ETH-09-16
Via አዲስ ማለዳ ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የታላቁ ህዳሴ ግድብ የግንባታ ወጪን ለመሸፈን ታስቦ ለህዝብ ሲቀርብ የነበረው የቦንድ ሽያጭ በ2010 ከነበረበት 2.14 ቢሊዮን ብር ከአንድ ቢሊዮን ብር በላይ በማሽቆልቆል በተገባደደው የ2011 በጀት ዓመት 970 ሚሊዮን ብር ብቻ ሆኖ ተመዘገበ።
የታላቁ ህዳሴ ግድብ ግንባታ ብሔራዊ አስተባባሪ ጽሕፈት ቤት የሚዲያ ግንኙነት ኀላፊ ኃይሉ አብርሃም ለአዲስ ማለዳ ጋዜጣ እንደገለፁት፣ በግድቡ መዘግየት እና ተያያዥ ችግሮች ምክንያት ህብረተሰቡ አመኔታ ማጣቱን እንደ ምክንያት ገልፀው ይህም የቦንዱን ሽያጭ አቀዛቅዞታል ብለዋል።
‹‹የህዳሴው ግድብ ግንባታ #ቆመ የሚል አመለካከት በመፈጠሩ ምክንያት ሀብት ከማሰባሰብ ይልቅ ማህበረሰቡ ጋር ያለውን የመረጃ ብዥታ ማጥራት ላይ ትኩረት አድርገን ስንሠራ ቆይተናል›› ሲሉም ተናግረዋል።
https://telegra.ph/ETH-09-16
Via አዲስ ማለዳ ጋዜጣ
@tsegabwolde @tikvahethiopia