TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#ሶማሌ

በሶማሌ ክልል የኢትዮጵያ #ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስትያን ፓትርያሪክ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ እና የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጦፋ ሙሀመድ ዑመር በተገኙበት የችግኝ ተከላ ሥነ-ስርዓት እየተካሄደ ነው።

Via #AMMA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ሶማሌ_ክልል

አልሸባብ የሽብር ቡድን ዳግም ድንበር አቋርጦ ለመግባት ሞክሮ በሶማሌ ክልል ልዩ ኃይል መታቱ ታውቋል።

የሶማሌ ክልል ልዩ ሀይል ሰራዊት ዛሬ ድንበር አቋርጦ ለመግባት የሞከረውን አሸባሪውን የአልሸባብ ታጣቂ ቡድን መደምሰሱን የክልሉ ኮሚኒኬሽን አሳውቋል።

ልዩ ሀይሉ የሽብር ቡድኑን ታጣቂዎች ከመደምሰስ ባለፈ በርካታ የጦርና የመገናኛ መሣሪያዎችን መያዝ ችሏል።

ወደ ውስጥ ለመግባት ከሞከሩ ታጣቂዎች መካከል የተማረኩም አሉበት።

አልሸባብ ከሶማሊያ ሂራን ግዛት ተነስቶ ነው ድንበር አቋርጦ ወደ ሸቤሌ ዞን ፌርፌር ወረዳ ለመግባት የሞከረው።

ነገር ግን በሶማሌ ልዩ ኃይል በደረሰበት ምት ኤል ቁዱን በምትባል ቦታ ላይ ተደምስሷል።

ከጥቂት ቀን በፊት ይህ የሽብር ቡድን ድንበር ጥሶ ሊገባ ቢሞክርም በሶማሌ ልዩ ኃይል ደረሰበት ከፍተኛ ምት ከ100 በላይ ታጣቂዎቹን እንዳጣ አይዘነጋም።

በሌላ በኩል የሶማሌ ክልል ህዝብ ለልዩ ኃይሉ እያደረገ ያለው ድጋፍና እገዛ እንደቀጠለ መሆኑን የክልሉ ኮሚኒኬሽን ገልጿል።

@tikvahethiopia
👍1.05K124👏86🙏48😢38🥰16
ለመላው የኢትዮጵያ ልጆች የቀረበ ጥሪ !

የ " ኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኅበር " በድርቅ ምክንያት ለጉዳት የተጋላጡ ወገኖችን ለመርዳት የሚያስችል የድጋፍ ማሰባሰቢያ ጥሪ አቅርቧል።

ማህበሩ ከቅርብ አመታት ወዲህ በደቡባዊና ደቡብ ምስራቃዊ አካባቢዎች የተከሰተው የድርቅ አደጋ በሰውና በእንስሶች ላይ ያስከተለውና እያስከተለ ያለው ጉዳት #እጅግ_አስከፊ መሆኑን ገልጿል።

ማኅበሩ እ.አ.አ በ2022 ከተለያዩ አጋር አካላት ጋር በመተባባር ፦
- በደቡብ ክልል ከንባታ ጠንባሮና ጋሞ ዞኖች፣
- በኦሮሚያ ክልል ቦረና፣ ባሌ፣ ምስራቅ ባሌ እና ምስራቅ ጉጂ ዞኖች፣
- በሶማሌ ክልል ሸበሌ፣ ፋፈን እና አፍዴር ዞኖች ከዚህ በተጨማሪ ሞያሌ አካባቢ በድርቅ አደጋ ምክንያት ለችግር የተጋለጡ 14,530 አባዎራዎችን ህይወት ለመታደግ ከ104 ሚሊዮን ብር በላይ የጥሬ ገንዘብ ድጋፍ አድርጓል።

በአሁኑ ወቅትም በተለይም #በኦሮሚያ እና #ሶማሌ ክልሎች እንዲሁም ሞያሌ አካባቢ በ206.3 ሚሊዮን ብር መሰል ድጋፍ ለማድረግ ቅድመ ዝግጅት እያደረገ ነው።

ድርቁ በሰውም ሆነ በእንስሶች ላይ እያስከተለ ካለው ጉዳት አንፃር እየተደረገ ያለው ድጋፍ በቂ ባለመሆኑ ማህበሩ የተጎጂዎችን ህይወት ለመታደግ እያደረገ ያለውን ጥረት መላው ኢትዮጵያውያን በአይነትም ሆነ በገንዘብ እንዲደግፉ ጥሪ አቅርቧል።

እንዴት ድጋፍ ማድረግ ይቻላል ?

1ኛ. #የአይነት_ድጋፍ ማድረግ የሚፈልጉ አዲስ አበባ ስቴዲየም አካባቢ በሚገኘው የማህበሩ ዋና መ/ ቤት ግቢ ድረስ በማምጣት መለገስ ይችላሉ።

2ኛ. የገንዘብ ልገሳ ማድረግ የሚፈልጉ በ #ቴሌ_ብር ሂሳብ ቁጥር 0907 ድጋፍ ማድረግ ይችላሉ።

3ኛ. ለቦረና ድርቅ ምላሽ ተብሎ በተከፈት የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ሂሳብ ቁጥር 👉 1000529766916 እንዲሁም 907 አጭር የሂሳብ ቁጥርን በመጠቀም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ፤ በዳሽን ባንክ፤ በአቢሲኒያ ባንክ፤ በአዋሽ ባንክ እና በኦሮሚያ ህብረት ሥራ ባንክ ገንዘብ ገቢ ማድረግ ይቻላል።

4ኛ. የእጅ ስልክ በመጠቀም በ9400 ላይ OK ብሎ በመላክ 1 ብር መለገስ ይቻላል።

#EthiopianRedCrossSociety
#ETHIOPIA🇪🇹

@tikvahethiopia
👍815👎58🙏33🕊24🥰2216😢10😱6🤔1
#ሶማሌ

በትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ህይወት ተቀጠፈ።

ዛሬ ከሰዓት በሶማሌ ክልል ፋፈን ዞን ፤ ሸበሌ ወረዳ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ህይወት ሲያልፍ 12 ሰዎች ተጎድተው ወደ ሆስፒታል ገብተዋል።

አደጋው የደረሰው ከጅግጅጋ መንገደኞችን አሳፍሮ ሲጓዝ በነበረ " ሚኒባስ " ተሽከርካሪ እና ከሸበሌ አቅጣጫ ሲመጣ በነበረ " ሲኖ ትራክ " እየተባለ በሚጠራው ተሽከርካሪ መካከል በተፈጠረ ግጭት ነው።

ፖሊስ የአደጋውን ምክንያት እያጣራ ሲሆን የሚደርስበትን ለህዝብ እንደሚያሳውቅ አመልክቷል።

የሶማሌ ክልል ፕሬዜዳንት ሙስጠፋ ሙሁመድ በትራፊክ አደጋው ምክንያት በጠፋው የሰው ህይወት የተሰማቸውን ጥልቅ ሀዘን ገልጸው ለቤተሰቦች፣ ለወዳጅ ዘመዶች መፅናናትን ተመኝተዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ከክልሉ ቴሌቪዥን (ኤስአርቲቪ ሶማልኛ) ማግኘቱን ያሳውቃል።

@tikvahethiopia
😭1.83K😢149129🕊94🙏55😱34🥰28😡17
TIKVAH-ETHIOPIA
#Afar #Somali #Iftar ዛሬ የአፋር እና ሶማሌ ወንድማማች ህዝቦች የኢፍጣር መርሐ ግብር በጅግጅጋ እየተካሄደ ይገኛል። በመርሃ ግብሩ የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳደር ሃጂ አወል አርባ፣ የሰላም ሚንስትሩ አቶ መሀመድ እድሪስ፣ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት ፕሬዝዳንት ሼኽ ሃጂ ኢብራሂም ቱፋን ጨምሮ ሌሎችም እንግዶች ተገኝተዋል። #SomaliRegionGovCommunication …
#አፋር 🕊 #ሶማሌ

" እኛ እና ሶማሌዎች ከሚያለያዩን ነገሮች ይልቅ አንድ የሚያደርጉን ነገሮች በትልቁ ይበዛሉ " - ሀጂ አወል አርባ

ዛሬ በአፋር ክልል መዲና ሠመራ የአፋር እና ሶማሌ ወንድማማች ሕዝቦች የኢፍጧር ስነስርዓት ተካሂዷል።

በስነ ስርዓቱ ላይ የሃይማኖት አባቶች፣ የእስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት አመራሮች፣ የሰላም ሚኒስትር አቶ መሐመድ እድሪስ  ፣ የሶማሌ ክልል ፕሬዜዳንት ሙስጠፋ ሙሁመድ እና ሌሎች የክልሉ ባለስልጣናት ተገኝተው ነበር።

የአፋር ክልል ፕሬዝዳንት ሀጂ አወል አርባ " እኛና ሶማሌዎች ከሚያለያዩን ነገሮች ይልቅ አንድ  የሚያደርጉን ነገሮች በትልቁ ይበዛሉ " ሲሉ ገልፀዋል።

ስነ ስርዓቱ የሁለቱን ክልል ወንድማማቾች የመተሳሰብ ፣ የአብሮነት እና የፍቅር ተምሳሌት ለማድረግ መካሄዱን ጠቁመዋል።

" ትላንት በሠው ሠራሽ ችግሮች የተፈጠሩትን ግጭቶችን ዛሬ የማስቆም ታሪካዊ ሀላፊነት የኛ ነው " ያሉ ሲሆን "  በኛ ትውልድ ከዚህ ቀደም ያለውን ጥላቻና መራራቅን የምንቀይርበትና የምናሻሽልበት ዘመን ነው " ብለዋል።

" ክፋትን ወደ ፍቅር እንቀይራለን ለዚህ ማሳያው ደግሞ የጅጅጋው እና የዛሬው የኢፍጣር ፕሮግራም ማሳያ ነው " ሲሉ ገልፀዋል።

የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ ሙሁመድ ፤ " ሁለታችንም ክልሎች በቀድሞው ስርዓት የተገፋን እና ከልማት የተገለልን ነበርን " ሲሉ ተደምጠዋል።

" በለውጡ ዘመን ያገኘነውን መሻሻል ተጠቅመን ከግጭት እና ከጥላቻ ወጥተን በአብሮነት ወደ ልማት እና ወደ ብልፅግና ተያይዘን እና ተደጋግፈን ያለንን የሠው ሀይል በጋራ በማድረግ ክልላችንን ማልማት አለብን " ሲሉ መግለጻቸውን የአፋር ብዙሃን መገናኛ ድርጅት ዘግቧል።

#AfarMassMediaAgency

@tikvahethiopia
758🕊111😡45🙏40👏18🤔17😭12😢9🥰5😱2