TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update በቅርቡ ግጭት በተከሰተባቸው የቤኒሻንጉል ጉሙዝ እና የኦሮሚያ ክልል አዋሳኝ ቦታዎች ላለፉት 2 ቀናት በአብዛኛዎቹ #መረጋጋት የታየባቸው ቢሆንም ሆሮ ሊሙና ያሶ በተባሉት ቦታዎች ግን አሁንም የፀጥታ ሥጋት መኖሩን የምሥራቅ ወለጋ ዞን የፀጥታ መምሪያ ኃላፊ አቶ ታከለ ቶሎሣ ለኢቲቪ ገልጸዋል፡፡ በአካባቢው ያለና #ማንነቱን በግልፅ ለመለየት ያልተቻለ የተደራጀ እና የታጠቀ ኃይል ሕዝቡን ሥጋት ውስጥ ከቶታል ያሉት ኃላፊው ችግሩን ለማስቆም መንግሥት አፋጣኝ እርምጃ ሊወስድ እንደሚገባው ተናግረዋል፡፡

@tsegabwolde @tikvahethiopia
" የሟች ኪስ ውስጥ #ማንነቱን የሚገልጽ መረጃ ስላላገኘን ፎቶውን ለማሰራጨት ተገደናል "  - የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ

በትግራይ ምስራቃዊ ዞን ዓዲግራት ከተማ  ቀበሌ 03 በተባለ መጠጥ ቤቶች በብዛት በሚገኙበት ቦታ ሚያዝያ 9/2016 ዓ.ም ሌሊት አሰቃቂ ግድያ ተፈፅሟል።

አስቃቂ ግድያው በመፈፀም የተጠረጠሩ 3 ግለሰቦች በህዝብ ጥቆማ የሟቹ አስከሬን በወደቀበት አከባቢ በሚገኝ መጠጥ ቤት በቁጥጥር ስር ውለው የሟች አስከሬን ወደ ዒድግራት ሆስፒታል ተወስደዋል።

የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ ምርመራው ጨርሶ ለቀብር የሟቹ ቤተሰብ ቢያፈላልግም ዜናው እስከ ተጠናቀረበት ቀን ሰዓትና ደቂቃ የሟች ቤተሰብ አልተገኙም።

በሟቹ ኪስ ማንነቱ የሚጠቅስ መረጃ እንዳላገኘ የገለፀው የዓዲግራት ፓሊስ ፤ የሟቹ ፎቶ በሚድያና በማህበራዊ የትስስር ገፅ ለማስራጨት መገደዱን ገልጿል።

ሟቹን የሚያውቅ ካለ ወደ ዓዲግራት ከተማ ፓሊስ ፅህፈት ቤት ደውሎ እንዲያሳውቅ ፖሊስ ትብብር ጠይቋል።

#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

ፍቶ፦ የዓዲግራት ከተማ ፓሊስ ፅህፈት ቤት 
                                             
@tikvahethiopia            
😭1.16K😢144103🕊46😡26😱18🙏17🥰10🤔4