TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.4K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#share #ሼር

በ2012 የትምህርት ዘመን ዩኒቨርሲቲ ለሚመደቡ ተማሪዎች በሙሉ፦

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ትምህርት ሚኒስቴር አገር አቀፍ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች ኤጀንሲ በ2012 የትምህርት ዘመን የሚካሄደው የተማሪዎች/ተፈታኞች ዩኒቨርሲቲ ምደባ በተፈጥሮ ሳይንስ፣ በማህበራዊ ሳይንስ እና በመምህርነት የሚካሔድ መሆኑን እያሳወቀ፣

1. ከተፈጥሮ ሳይንስ ወደ ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስክ መቀየር የተፈቀደ ሲሆን ከተፈጥሮ ሳይንስ ወደ ማህበራዊ ሳይንስ መቀየር የሚቻለው ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች /ተፈታኞች የተዘጋጀውን መቁረጫ/ማለፊያ/ ነጥብ ለሚያሟሉ ተማሪዎች ብቻ መሆኑን

2. የትምህርት መስክ ምርጫ፣
• ለተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች (ተፈታኞች) ፣ ተፈጥሮ ሳይንስና መምህርነት
• ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች (ተፈታኞች) ደግሞ ማህበራዊ ሳይንስና እና መምህርነት ብቻ እንዲሆን መወሰኑን

3. ተማሪዎች/ተፈታኞች ውጤታችሁን መሰረት በማድረግ የዩኒቨርሲቲ ምርጫችሁን ማስተካከል (መቀየር) የምትችሉ መሆኑን እየገለፀ

የዩኒቨርሲቲ ምርጫችሁን #ማስተካከል ሆነ የትምህርት መስክ መቀየር (ከተፈጥሮ ሳይንስ ወደ ማህበራዊ ሳይንስ) የሚቻለው በተማራችሁበት ትምህርት ቤት (ፈተና በወሰዳችሁበት የፈተና ጣቢያ) በኩል መሆኑን እያሳወቀ የዩኒቨርሲቲ ምርጫ ማስተካከያና የፊልድ መቀየሪያ ቀናት እስከ መስከረም 12/2012 ዓ.ም. ድረስ ብቻ ነው፡፡ የመሰናዶ ትምህርት ቤቶችም የተማሪዎችን ምርጫ ማስተካከልና የትምህርት መስክ ቅየራ/ ከተፈጥሮ ሳይንስ ወደ ማህበራዊ ሳይንስ/ ጥያቄ በመቀበል እንዲታስተናግዱ ያሳስባል፡፡

የኢ.ፌ.ዲ.ሪ. ትምህርት ሚኒስቴር
@tsegabwolde @tikvahethiopia