TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.3K photos
1.62K videos
218 files
4.4K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
ሚካኤል አፅብሃ ገብሩ⬆️ በአራዳ ክ/ከተማ ፒያሳ በተለምዶ መሀሙድ ሙዚቃ ቤት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የተገደለው ሚካኤል አፅብሃ ገብሩ ካላይ በፎቶው የምትመለከቱት ነው። ከካናዳ/ቶሮንቶ/ ወደኢትዮጵያ የመጣውም በቅርቡ ነበር። አቶ ሚካኤል ከአመት በፊት በካናዳ ሀገር የሎተሪ እድለኛ ሆኖ እንደነበር ወዳጆቹ ገልፀዋል። @tsegabwolde @tikvahethiopia
በአቶ #ሚካኤል_አፅብሃ_ገብሩ የግድያ ወንጀል የተጠረጠሩ ተጠርጣሪዎች መያዛቸው ተሰምቷል!

በአራዳ ክ/ከተማ ፒያሳ በተለምዶ መሀሙድ ሙዚቃ ቤት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ የግድያ ወንጀል የፈፀሙ ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያጣራ መሆኑን የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

መስከረም 3 ቀን 2012 ዓ.ም በግምት ከሌሊቱ 6 ሰዓት ሲሆን በአራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 01 ፒያሳ ልዩ ቦታው መሀሙድ ሙዚቃ ቤት ተብሎ በሚጠራው አካባቢ በአቶ ሚካኤል አጽበኻ ገብሩ ላይ የግድያ ወንጀል ፈፅመዋል ተብለው የተጠረጠሩ 2 ግለሰቦችን ይዞ ምርመራ እያጣራመ ሆኑን የአ/አበባ ፖሊስ ኮሚሽን አስታውቋል፡፡

ኮሚሽኑ እንደገለፀው ብዛታቸው 3 የሆኑ ተጠርጣሪዎች በዕለቱ ሟች ሚካኤል አፅበኻ ከጓደኛቸው ጋር እየተዝናኑ ከቆዩ በኋላ ወደ ማደሪያቸው ለመሄድ ታክሲ እየጠበቁ በነበሩበት አጋጣሚ ንብረት ለመዝረፍ በማሰብ ጉዳት አድርሰውባቸው ህይወታቸው እንዲያልፍ አድርገዋል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የወንጀሉ መፈፀም ሪፖርት እንደደረሰው ከአካባቢው ህብረተሰብ ጋር በመተባበር ቀንና ሌሊት ባደረገው ብርቱ ጥረት 48 ሰዓት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ ከተጠርጣሪዎቹ መካከል ሁለቱን በ05/01/2012 ዓ.ም ማምሻውን በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያጣራ መሆኑንና ቀሪውን አንድ ተጠርጣሪ ለመያዝ ክትትሉ መቀጠሉን አስታውቋል፡፡

ህብረተሰቡ ወንጀልፈፃሚዎቹ እንዲያዙ ላደረገው ቀና ትብብር ምስጋናውን በማቅረብ ወንጀልን የመከላከል ስራ ላይ የሚሰጠውን ድጋፍና ተሳትፎን አጠናክሮ አንዲቀጥል የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን ጥሪውን አስተላልፏል፡፡

ምንጭ፦ አ/አ ፖሊስ ኮሚሽን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1