TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
ፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን⬆️የሰላም ሚኒስትሯ ወይዘሮ #ሙፈሪያት_ከሚል ዛሬ የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽንን ጎብኝተዋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ወ/ሮ #ሙፈሪያት_ከሚል

"በሰላም ሚኒስትር እና የደህዴን ሊቀመንበሯ ሙፈርያት ካሚል ላይ የግድያ ሙከራ ተደረገ" ተብሎ እየተሰራጨ የሚገኘው መረጃ እውነትነት የራቀ መሆኑ የሰላም ሚኒስቴር የኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር ሄርሜላ ሰለሞን ለአለም አቀፉ ጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ተናገሩ። ዳይሬክተሯ ወሬውን ለማጣራት ወ/ሮ ሙፈርያት ጋር ከደወሉ በሁዋላ ይህንን ብለዋል፦

"ሚኒስትሯ ቀኑን ሙሉ ሀዋሳ ስብሰባ ላይ ነው የዋሉት። እንኳን ሙከራ ሊደረግ ለመሞከር እድል የሚኖርበት ሁኔታ አልነበረም። ለማንኛውም የተባለው ሙሉ ለሙሉ #ውሸት ነው ብለው ሚኒስትሯ እራሳቸው አሁን በስልክ ነግረውኛል። ምንም የተለየ ነገር አልተፈጠረም።"

ከዚህ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ አንድ የክልሉ ባለስልጣን መረጃው ፌክ ኒውስ ነው ሲሉ ለጋዜጠኛ ኤልያስ መሰረት ተናግረዋል።

@tsegabwolde @tikvahethuopia