TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#MoE

ትምህርት ሚኒስቴር ፤ በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ይማሩ የነበሩና በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው ለተመረቁ ተማሪዎች #መደበኛ_ዲግሪ ለመስጠት እንደሚቸገር አሳውቋል፡፡

በትግራይ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ይማሩ የነበሩና በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ተመድበው ትምህርታቸውን ያጠናቀቁ ከአራት ሺህ በላይ ተማሪዎች መደበኛ ዲግሪ ማግኘት ባለመቻላቸው ሥራ ለመቀጠር መቸገራቸውን ይገልጻሉ።

በተማሪዎቹ ቅሬታ ዙሪያ በሪፖርተር ጋዜጣ የተጠየቁት የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) " የተማሪዎቹ ሙሉ መረጃ ሳይገኝ መደበኛ ዲግሪ ለመስጠት እንደሚቸገሩ " ገልጸዋል።

" ሰላምና መረጋጋት በሰሜን ኢትዮጵያ በአስተማማኝ ሁኔታ ሲሰፍን ከመጡባቸው ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርት ያቆሙበት መረጃ ተሟልቶ ሲቀርብ ዲግሪው ይሰጣቸዋል " ሲሉ አክለዋል፡፡

እስከዚያው ግን በተሰጣቸው ጊዚያዊ ሰርተፊኬት ሥራ መፈለግ እንደሚችሉ ነው ሚኒስትሩ የተናገሩት።

በትግራይ ክልል ከሚገኙ ዩኒቨርሲቲዎች ተፈናቅለው በሌሎች ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን ያጠናቀቁት ተማሪዎች ግን " ትምህርት ሚኒስቴር በአንድ ሴሚስተር የውጤት መግለጫ ወረቀት/Grade Report አሰናብቶናል " ሲሉ ቅሬታቸውን አሰምተዋል፡፡

ይህ ወረቀት በሥራ ዓለም ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቀጠር እንደማያስችላቸው በመጥቀስ ሚኒስቴሩ ዘላቂ መፍትሄ እንዲፈልግላቸው ጠይቀዋል፡፡

@tikvahuniversity @tikvahethiopia
👍2