TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የእሳት አደጋ ፦

#ሐረማያ_ዩኒቨርሲቲ

በሐረማያ ዩኒቨርሲቲ ዋናው ግቢ ህንፃ 3 የሚባለው የድህረ ምረቃ ተማሪዎች ከሚኖሩበት ህንፃ የኤሌክትሪክ መቆጣጠሪያ ላይ የተነሳ የእሳት አደጋ በቁጥጥር ስር ውሏል።

በእሳት አደጋው በንብረት ላይ ጉዳት ያደረሰ ቢሆንም በሰው ላይ ምንም ጉዳት አለማድረሱን የዩኒቨርሲቲው ሕዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት አስታውቋል።

#መካነ_ሠላም_ከተማ

በደቡብ ወሎ ዞን መካነሠላም ከተማ ድንገት የተከሰተ የእሳት አደጋ በንብረት ላይ ጉዳት አድርሷል።

መንስኤው ያልታወቀው የእሳት አደጋ በግምት ከለሊቱ 8፡00 ሰዓት አካባቢ የተከሰተ ሲሆን በሸቀጣ ሸቀጥ ሱቆች ላይ ፣ በሴቶች የውበት ሳሎን እና በልብስ ስፌት ቤቶች ላይ ነው ጉዳት ያደረሰው፡፡

ከአምስት (5) በላይ ሱቆች እና ሌሎች የገበያ ቤቶች በእሳት አደጋው የተጎዱ ሲሆን የሱቅ እቃዎች ፣ የተለያዩ ማሽኖች እና ከ1 መቶ ሺህ ብር በላይ ጥሬ ገንዘብ ተቃጥሏል፡፡

Via @TIKVAHETHMAGAZINE

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia