TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የአፍሪካ ህብረት አስቸኳይ ጉባኤ‼️

የአፍሪካ ኅብረት ከሕዳር 8-9 ቀናት 2011ዓ.ም በአዲስ አበባ ለሚያደርገው አስቸኳይ ጉባኤ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዝግጅት #ማጠናቀቁን አስታውቋል፡፡

ኢትዮጵያ 11ኛው የርዕሳን ብሔራት እና ርዕሳነ መንግሥታት አስቸኳይ ጉባኤዎችን በውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች ደረጃ ከሕዳር 5-6 ቀናት 2011ዓ.ም እና በመሪዎች ደረጃ ደግሞ ከሕዳር 8-9 ቀናት 2011 ዓ.ም ለምታዘጋጀው ጉባኤ ሙሉ ዝግጅት ማጠናቀቋን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ያደረሰን መረጃ ያመለክታል፡፡

የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አቶ #መለስ_ዓለም እንዳስታወቁት የጉባኤው ዓላማ የአፍሪካ ኅብረት ኮሚሽን አዲስ ማሻሻያን የሚመለከት ነው ተብሏል፡፡

በጉባኤው ከ45 በላይ ሀገራት እንደሚሳተፉ ማረጋገጫ ሰጥተዋል፡፡ ለዝግጅቱ ከ40 በላይ መሥሪያ ቤቶች ከኤርፖርት ጀምሮ እስከ ሆቴል እና መሰብሰብያ ጉበኤው ድረስ ያሉ አሠራሮችን ቀላል ለማድረግ እየሠሩ እንደሆነም ታውቋል፡፡

ከ79 በላይ ደረጃቸውን የጠበቁ ሆቴሎችም ለእንግዶች ማረፊያ ዝግጁ መሆናቸው ተገልጿል፡፡

ምንጭ፦ አብመድ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update “የኢትዮጵያን በጎ ገፅታ′ በፎቶግራፊ ሙያ ለዓለም ለማስተዋወቅ እንደሚሰሩ የእውቁ ኬንያዊ ፎቶ ጋዜጠኛ መሐመድ አሚን ልጅ ሳሊም አሚን ገለፁ። ሳሊም አሚን በናይሮቢ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ተገኝተው ከሚሲዮኑ ጋር በመተባበር “የኢትዮጵያን በጎ ገፅታ′ በፎቶግራፊ ሙያ ለዓለም ማስተዋወቅ በሚቻልባቸው ሁኔታዎች ላይ ከአምባሳደር #መለስ_ዓለም ጋር መክረዋል።

Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia