TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
AASTU🔝ዶክተር #ሂሩት_ወልደማርያም በተለያዩ ጉዳዮች ዙሪያ ከአዲስ አበባ ሳይንስ እና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ጋር እየተወያዩ ይገኛሉ።

ፎቶ፦ አማኑኤል(TIKVAH-ETH)
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት‼️

በሁሉም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሠላማዊ የመማር ማስተማር ሂደት #ተጠናክሮ መቀጠሉን የሳይንስና የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ሚኒስቴር ገለጸ።

ሚኒስትሯ ፕሮፌሰር #ሂሩት_ወልደማርያም ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት እንደተናገሩት፤ በአሁኑ ወቅት በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች ሠላማዊው የመማር ማስተማር ሂደቱ ተጠናክሮ ቀጥሏል።

ከዚህ ቀደም ችግሮች ይስተዋሉባቸው የነበሩ ዩኒቨርሲቲዎች ያሉባቸውን ችግሮች አመራሮቻቸው የተለያዩ እርምጃዎችን በመውሰድ ለመፍታት ተሞክሯል ብለዋል።

ተማሪዎችም የእረፍት ጊዜ እንዲወስዱ በማድረግም ችግሮቹን ለማርገብ መሰራቱን ገልጸው፤ ሠላሙን ዘላቂ ለማድረግም የተማሪዎች አመለካከት ላይ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

ተማሪዎቹን ሊያነቃቁ የሚችሉ ንግግሮች እንዲሁም የተለያዩ ውይይቶችም በተለይም ከታዋቂ ግለሰቦች ጋር በሁሉም ዩኒቨርሲቲዎች እየተደረጉ መሆኑን ጠቁመዋል።

ጎን ለጎንም በአመለካከተ ላይ አዎንታዊ ለውጥ ሊያመጡ የሚችሉ ድራማና ሌሎች የጥበብ ሥራዎችም በስፋት እየተሰሩ መሆኑን ገልጸዋል።

ተማሪዎች ከኅብረተሰቡ ጋር ያላቸውን ግንኙነት እንዲያጠናክሩ ለማድረግም የበጎ አድራጎት ሥራ ላይ ተሳታፊ እንዲሆኑም መደረጉን ሚኒስትሯ አስረድተዋል።

ይህም ደግሞ ተማሪዎች ዓላማቸውን በደንብ አጥብቀው እንዲይዙ በማድረግ በየትኛውም ኃይል ተጠልፈው እንዳይወድቁ ለማድረግ ሚናው የጎላ መሆኑን ተናግረዋል። በአሁኑ ወቅት በኢትዮጵያ 45 የመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ይገኛሉ።

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia