TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ይህ የሰላም ጥረት ወደ ሌሎችም የሀገሪቱ ክፍሎች ይስፋፋ " - አቶ ጃዋር መሀመድ

የኦሮሞ ፌዴራሊስት ኮንግረስ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ጃዋር መሐመድ ከደቡብ አፍሪካ፤ የተሰማው ዜና አበረታች መሆኑን ገልፀው የኢትዮጵያ መንግሥት እና ህወሓት እንዲሁም አደራዳሪዎችና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት በፍጥነት የሰላም ስምምነቱን ተፈጸሚ እንዲያደርጉ ጥሪ አቅርበዋል።

" ይህ የሰላም ጥረት ወደ ሌሎችም የሀገሪቱ ክፍሎች ይስፋፋ " ያሉት አቶ ጃዋር በተለይ ጦርነት እየተካሄደባት ነው ባሉት የኦሮሚያ ክልል ልዩነቶች በድርድር እንዲፈቱ እና በመላው ሀገሪቱ ሰላም እንዲሰፍን ጥረት እንዲደረግ ጥሪ አቅርበዋል።

በመልዕክታቸው #ሁሉን_አቀፍ_ሰላም ለኢትዮጵያ እንደሚያስፈልግ ነው ያስገነዘቡት።

በደቡብ አፍሪካ ለተደረሰው የሰላም ስምምነት ፤ ተደራዳሪ ቡድኖችን ፣ የአፍሪካ ህብረት (AU) አሸማጋዮችን ፣ ታዛቢዎች እና አስተናጋጇን ሀገር ደቡብ አፍሪካ አመስግነዋል።

አቶ ጃዋር መሀመድ ሀገራችንን እና ህዝባችንን ከከፋ እልቂት ለመታደግ አሁን እየታየ ባለው በዚህ የሰላም መነቃቃት እንስራ ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።

@tikvahethiopia
👍2.86K👎548🕊531278🙏103😢31😱30