#እንድታውቁት
አዲስ አበባ ውስጥ አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ይዞ መገኘት አስገዳጅ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት ከዛሬ ታህሳስ 23 , 2017 ዓ.ም (Jan 1st 2025) ጀምሮ በአዲስ አበባ በሚገኙ በሁሉም ባንኮች አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ (የፋይዳ ቁጥር) ይዞ መቅረብ እንደ መጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ ሆኗል።
በሌላ ተያያዥ መረጃ ...
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ " ፋይዳን ለባንክ አገልግሎት አስገዳጅነት " ትዕዛዝ ወደ ትግበራ መግባት ተከትሎ የተለያዩ ባንኮች የማርኬቲንግ እና ኮርፖሬት ህዝብ ግንኙነት ከፍተኛ ሀላፊዎች ያሳተፈ በጥምረት ግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ በይፋ መጀመሩን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አሳውቆናል።
ከኃላፊዎች ጋር በነበረ ውይይት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ዮዳሔ አርአያስላሴ ፤ " የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ባንኮች በፋይዳ መታወቂያ ዙሪያ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን ልክ እንደ አንድ የባንክ አገልግሎት አጽንዖት ተሰጥቶት እንዲሰሩ " ሲሉ አሳስበዋል።
#ፋይዳለኢትዮጵያ #መታወቅ #አካታች #DigitalID
@tikvahethiopia
አዲስ አበባ ውስጥ አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት ፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ይዞ መገኘት አስገዳጅ ሆኗል።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባወጣው መመሪያ መሠረት ከዛሬ ታህሳስ 23 , 2017 ዓ.ም (Jan 1st 2025) ጀምሮ በአዲስ አበባ በሚገኙ በሁሉም ባንኮች አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ (የፋይዳ ቁጥር) ይዞ መቅረብ እንደ መጀመሪያ ቅድመ ሁኔታ ተግባራዊ ሆኗል።
በሌላ ተያያዥ መረጃ ...
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ " ፋይዳን ለባንክ አገልግሎት አስገዳጅነት " ትዕዛዝ ወደ ትግበራ መግባት ተከትሎ የተለያዩ ባንኮች የማርኬቲንግ እና ኮርፖሬት ህዝብ ግንኙነት ከፍተኛ ሀላፊዎች ያሳተፈ በጥምረት ግንዛቤ ማስጨበጫ ዘመቻ በይፋ መጀመሩን የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አሳውቆናል።
ከኃላፊዎች ጋር በነበረ ውይይት የብሔራዊ መታወቂያ ፕሮግራም አስተባባሪ አቶ ዮዳሔ አርአያስላሴ ፤ " የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት ባንኮች በፋይዳ መታወቂያ ዙሪያ ግንዛቤ የማስጨበጥ ስራዎችን ልክ እንደ አንድ የባንክ አገልግሎት አጽንዖት ተሰጥቶት እንዲሰሩ " ሲሉ አሳስበዋል።
#ፋይዳለኢትዮጵያ #መታወቅ #አካታች #DigitalID
@tikvahethiopia
😡1.1K🙏169❤108👏91🤔39😭38🕊20😢19🥰17😱17
ADDIS ABABA NO 3 Total Tax Payers.pdf
6.4 MB
#እንድታውቁት
" 12 ሺ ለሚሆኑ ግብር ከፋዮች የታክስ መክፈያ ማዕከል ቅያሪ ተደርጓል " - የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥን ተደራሽ ለማድረግ እና ካለው የተገልጋይ ብዛት አኳያ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስቸግር በመሆኑ ለ12 ሺህ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ክፍያ ማዕከል (Tax Center) ቦታ ቅያሪ ማድረጉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የቢሮው የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ " የቦታ ቅያሪው የተደረገው በቦታው የበርካታ ግብር ከፋዮች ጫና በመኖሩ የተወሰነውን በመቀነስ ግብር ከፋዩ በአቅራቢያው ማግኘት የሚችልበትን እድል ለመፍጠር ነው " ብለዋል።
ቅያሪው የተደረገው ከስታዲየም አካባቢ የሃ ህንፃ ወደ ጉርድ ሾላ ከሳሊተ ምህረት ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት ወደሚገኘው ሜሪዲያን ኮንቬሽን ሴንተር ነው።
በአዲስ አበባ 11 የአንስተኛ ፣ 5 የመካከለኛ እና 1 የከፍተኛ ግብር ከፋይ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የሚገኙ ሲሆኑ የአሁኑ 17ኛው ቅርንጫፍ ነው ተብሏል።
የቦታ ቅያሪው የሚመለከታቸው ተገልጋዮች ስማቸውን ከላይ በተያያዘው ፋይል በመመልከት ከጥር 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
" 12 ሺ ለሚሆኑ ግብር ከፋዮች የታክስ መክፈያ ማዕከል ቅያሪ ተደርጓል " - የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ
የአዲስ አበባ ገቢዎች ቢሮ የአገልግሎት አሰጣጥን ተደራሽ ለማድረግ እና ካለው የተገልጋይ ብዛት አኳያ ቀልጣፋ አገልግሎት ለመስጠት የሚያስቸግር በመሆኑ ለ12 ሺህ የመካከለኛ ግብር ከፋዮች የታክስ ክፍያ ማዕከል (Tax Center) ቦታ ቅያሪ ማድረጉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገልጿል።
የቢሮው የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ሰውነት አየለ " የቦታ ቅያሪው የተደረገው በቦታው የበርካታ ግብር ከፋዮች ጫና በመኖሩ የተወሰነውን በመቀነስ ግብር ከፋዩ በአቅራቢያው ማግኘት የሚችልበትን እድል ለመፍጠር ነው " ብለዋል።
ቅያሪው የተደረገው ከስታዲየም አካባቢ የሃ ህንፃ ወደ ጉርድ ሾላ ከሳሊተ ምህረት ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት ወደሚገኘው ሜሪዲያን ኮንቬሽን ሴንተር ነው።
በአዲስ አበባ 11 የአንስተኛ ፣ 5 የመካከለኛ እና 1 የከፍተኛ ግብር ከፋይ ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶች የሚገኙ ሲሆኑ የአሁኑ 17ኛው ቅርንጫፍ ነው ተብሏል።
የቦታ ቅያሪው የሚመለከታቸው ተገልጋዮች ስማቸውን ከላይ በተያያዘው ፋይል በመመልከት ከጥር 1/2017 ዓ/ም ጀምሮ አገልግሎት ማግኘት ይችላሉ ተብሏል።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
❤104😡62🙏12🤔11🕊10😱7😭5👏4🥰2