TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
የቤጂንግ እና የዋሽንግቶን ውጥረት ? አሜሪካ እና ቻይናን ውጥረት ውስጥ የከተታቸው የታይዋን ጉዳይ ነው። ቻይና ታይዋን #ወደ_እናት_አገሯ መመለስ ያለባት አፈንጋጭ ግዛቷ እንደሆነች ነው የምታስበው ይህንንም ለማሳካት ወደፊት ቤይጂንግ ኃይል መጠቀምን እንደ አንድ አማራጭ ታየዋለች።  አሜሪካ ደግሞ ከቻይና ጋር ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት ያላት ሲሆን፣ ከታይዋን ጋር ግን “ይፋዊ ያልሆ ጠንካራ” ዲፕሎማሲያዊ…
" ሀሰተኛ ዜና ነው " - ታይዋን

የታይዋን መከላከያ የቻይና የጦር ጄቶች PLA Su-35 " የታይዋንን አየር ክልል ጥሰው ገቡ " ተብሎ በኦንላይን ሚዲያዎች የሚሰራጨው መረጃ #ሀሰተኛ_ዜና ነው አለ።

በታይዋን ያለውን ጉዳይ የሚከታተሉ ትክክለኛው የመከላከያ ድረገፅ ብቻ እንዲጠቀሙ መልዕክት አስተለልፏል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ ነዋሪዎች በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩትን ሀሰተኛ መረጃዎች ለሌሎች እንዳያጋሩ አሳስቦ " ይህን እኩይ ተግባር በጽኑ እናወግዛለን " ብሏል።

CGTNን ጨምሮ ሌሎችም ሚዲያዎች የቻይና Su-35 ተዋጊ ጄቶች " የታይዋንን አየር ክልል ጥሰው ገቡ " ሲሉ ዘገባዎችን አውጥተው ነበር።

ቻይና " ታይዋን " #ወደ_እናት_ሀገሯ መመለስ አለባት ብላ ታምናለች ፤ ታይዋንን የሚደግፉ ሁሉ በሀገር አንድነት ላይ አደጋ ያመጡ አድርጋ ነው የምትወስዳቸው።

ለዛም ነው በአሜሪካ የስልጣን እርከን ሶስተኛዋ ሰው ፔሎሲ ታይዋን መግባታቸው ያስቆጣት እና እርምጃ እንደምትወስድ በተደጋጋሚ እየዛተች የምትገኘው።

@tikvahethiopia
👍919👎64🙏4341😢31🥰15👏15
TIKVAH-ETHIOPIA
" ሀሰተኛ ዜና ነው " - ታይዋን የታይዋን መከላከያ የቻይና የጦር ጄቶች PLA Su-35 " የታይዋንን አየር ክልል ጥሰው ገቡ " ተብሎ በኦንላይን ሚዲያዎች የሚሰራጨው መረጃ #ሀሰተኛ_ዜና ነው አለ። በታይዋን ያለውን ጉዳይ የሚከታተሉ ትክክለኛው የመከላከያ ድረገፅ ብቻ እንዲጠቀሙ መልዕክት አስተለልፏል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ነዋሪዎች በማህበራዊ ሚዲያ የሚሰራጩትን ሀሰተኛ መረጃዎች ለሌሎች እንዳያጋሩ…
#Update

ፔሎሲ የታይዋን ጉብኝታቸውን አጠናቀው ታይዋንን ለቀው ወጥተዋል።

የአሜሪካ ምክር ቤት አፈ ጉባኤ እና በሀገሪቱ የስልጣን እርከን ሶስተኛ ሰው የሆኑት ናንሲ ፔሎሲ ታይዋን ጎብኝተዋል።

ትላንት ታይዋን ሲደርሱ አቀባበል ተደርጎላቸዋል።

የፔሎሲ የታይዋን ጉብኝት ብዙ ሲባልለት የነበረ እና በአሜሪካ እና ቻይና መካከል የፈጠረው ከፍተኛ ውጥረት ዓለምን ያሰጋ ነበር።

ቻይና ፔሎሲ ወደታይዋን እንደሚመጡ ከሰማች ጊዜ አንስታ ስታስጠነቅቅና እስከወታደራዊ እርምጃ ድረስ እንደምትወስድ ፤ አሜሪካም ትልቅ ዋጋ እንደምትከፍል ስትዝት ነበር።

ነገር ግን ፔሎሲ ወደ ታይዋን ገብተው ጉብኝትም አድርገው ፤ ማግኘት ያለባቸውን አካላት ባለስልጣናት አግኝተው ዛሬ ታይዋንን ለቀው ወጥተዋል።

ቻይና ጉብኝቱን ለማስቆም የወሰደችው ምንም እርምጃ ባይኖርም በአካባቢው ላይ ግን ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ስለመኖራቸው ታውቋል።

ትላንት የቻይና የጦር ጄቶቿ ወደ ታይዋይን የአየር ክልል ዘልቀው መግባታቸው በኦንላይ ሚዲያ ቢሰራጭም መረጃው ውሸት እንደነበር የታይዋን መከላከያ ማሳወቁ ይታወሳል።

ቻይና " ታይዋን " የራሷ ግዛት አድርጋ ነው የምታስባት ፤ #ወደ_እናት_ሀገሯ መመለስ አለባትም ብላ ታምናለች ለዚህም ታይዋንን የሚደግፉ ሁሉ በሀገር አንድነት ላይ አደጋ ያመጡ አድርጋ ነው የምትወስዳቸው።

@tikvahethiopia
👍923👎12641👏29🥰28🙏21😢10