#update ፌደራል ፖሊስ⬇️
የህዝቡን #ደህንነት እና #ሰላም ለመጠበቅ ሲል መንግስት አስፈላጊውን #እርምጃ እንደሚወስድ የፌደራል ፖሊስ ገለፀ።
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ከሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸው ላይ የመንግስት ትእግስት #ገደብ እንዳለው በመግለፅ #ጉልበተኞችን እንደማይታገስ አስታውቀዋል።
አሁን ላይ እየተስተዋሉ ያሉት #ሁከቶች #በሁለት የፖለቲካ ድርጅቶች ስም የተቀነባበሩ መሆናቸውን ኮሚሽነር ጀነራሉ ጠቁመዋል።
ባለፉት ሦስት ቀናት በቡራዩና አካባቢው ብዛት ያላቸው ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን በመጠቆም፥ በተለያዩ ቦታዎች ተዘርፈው የነበሩ ንብረቶችን የማሰባሰብ ስራ መሰራቱንም ነው ያስታወቁት።
በአጠቃላይም በቡራዩ ከ300 አስከ 400 የሚደርሱ ተጠርጣሪዎች ሲያዙ በአዲስ አበባ ደግሞ ከ300 በላይ ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን ገልጸዋል፡፡
በአዲስ አበባ #ገንዘብ ተከፍሏቸው ብሄርን ከብሄር ለማጋጨት እንዲሁም ብሄርን መሰረት ያደረጉ ስድቦችንም ጭምር በማሰራጨት #የተጠረጠሩ ግለሰቦች መያዛቸውንም አንስተዋል።
ይህ ድርጊት #በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባና በአርባ ምንጭ መታየቱን ጠቅሰዋል።
ኮሚሽነሩ በቡራዩና አካባቢው የተፈፀመውን ግድያ ለማውገዝ በርካታ ሰላማዊ ሰው መውጣቱን ጠቅሰው #የተወሰኑ ቡድኖች ግን አዝሚሚያቸው ሌላ ነበር ብለዋል።
ከእነዚህ የተወሰኑ ግለሰቦች መካከልም #ቦምብ ይዘው የነበሩ በህብረተሰቡ ትብብር መያዛቸውን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በፒያሳና በመርካቶ #ለዝርፊያ የሚቃጡ ግለሰቦች እንደነበሩ ነው የጠቀሱት።
የተወሰኑት የጸጥታ ኃይሎች ደግሞ ጠብመንጃ ለመንጠቅ ሙከራ ያደረጉ ሲሆን በዚህም ከጸጥታ ኃይሉ ጋር #ግብግብ ገጥመው ነበር ብለዋል።
ይህንንም ተከትሎ የአምስት ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን፥ ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች መቁሰላቸውን ገልጸዋል።
በአጠቃላይ ይህ ግርግር ሆን ተብሎ የተጀመረውን ለውጥ #እንዳይሳካ #ታስቦበት የተከናወነ መሆኑን ነው ያነሱት።
©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የህዝቡን #ደህንነት እና #ሰላም ለመጠበቅ ሲል መንግስት አስፈላጊውን #እርምጃ እንደሚወስድ የፌደራል ፖሊስ ገለፀ።
የፌደራል ፖሊስ ኮሚሽን ከሚሽነር ጀነራል ዘይኑ ጀማል በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ዛሬ መግለጫ ሰጥተዋል።
በመግለጫቸው ላይ የመንግስት ትእግስት #ገደብ እንዳለው በመግለፅ #ጉልበተኞችን እንደማይታገስ አስታውቀዋል።
አሁን ላይ እየተስተዋሉ ያሉት #ሁከቶች #በሁለት የፖለቲካ ድርጅቶች ስም የተቀነባበሩ መሆናቸውን ኮሚሽነር ጀነራሉ ጠቁመዋል።
ባለፉት ሦስት ቀናት በቡራዩና አካባቢው ብዛት ያላቸው ወንጀለኞች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን በመጠቆም፥ በተለያዩ ቦታዎች ተዘርፈው የነበሩ ንብረቶችን የማሰባሰብ ስራ መሰራቱንም ነው ያስታወቁት።
በአጠቃላይም በቡራዩ ከ300 አስከ 400 የሚደርሱ ተጠርጣሪዎች ሲያዙ በአዲስ አበባ ደግሞ ከ300 በላይ ተጠርጣሪዎች መያዛቸውን ገልጸዋል፡፡
በአዲስ አበባ #ገንዘብ ተከፍሏቸው ብሄርን ከብሄር ለማጋጨት እንዲሁም ብሄርን መሰረት ያደረጉ ስድቦችንም ጭምር በማሰራጨት #የተጠረጠሩ ግለሰቦች መያዛቸውንም አንስተዋል።
ይህ ድርጊት #በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባና በአርባ ምንጭ መታየቱን ጠቅሰዋል።
ኮሚሽነሩ በቡራዩና አካባቢው የተፈፀመውን ግድያ ለማውገዝ በርካታ ሰላማዊ ሰው መውጣቱን ጠቅሰው #የተወሰኑ ቡድኖች ግን አዝሚሚያቸው ሌላ ነበር ብለዋል።
ከእነዚህ የተወሰኑ ግለሰቦች መካከልም #ቦምብ ይዘው የነበሩ በህብረተሰቡ ትብብር መያዛቸውን ገልጸዋል።
ከዚህ በተጨማሪም በፒያሳና በመርካቶ #ለዝርፊያ የሚቃጡ ግለሰቦች እንደነበሩ ነው የጠቀሱት።
የተወሰኑት የጸጥታ ኃይሎች ደግሞ ጠብመንጃ ለመንጠቅ ሙከራ ያደረጉ ሲሆን በዚህም ከጸጥታ ኃይሉ ጋር #ግብግብ ገጥመው ነበር ብለዋል።
ይህንንም ተከትሎ የአምስት ሰዎች ህይወት ያለፈ ሲሆን፥ ቁጥራቸው ያልታወቁ ሰዎች መቁሰላቸውን ገልጸዋል።
በአጠቃላይ ይህ ግርግር ሆን ተብሎ የተጀመረውን ለውጥ #እንዳይሳካ #ታስቦበት የተከናወነ መሆኑን ነው ያነሱት።
©fbc
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠ/ሚ ዶ/ር አብይ🔝
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #ዐቢይ_አሕመድ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ #በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ መሪዎች ከፍተኛ የምክክር ስብሰባ ላይ ተሳትፈዋል፡፡
via epa
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር #ዐቢይ_አሕመድ የዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ኮንጎን ወቅታዊ ሁኔታ አስመልክቶ #በዛሬው ዕለት በአዲስ አበባ በተካሄደው የአፍሪካ መሪዎች ከፍተኛ የምክክር ስብሰባ ላይ ተሳትፈዋል፡፡
via epa
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የትራፊክ አደጋ...
#አርባምንጭ
በአርባምንጭ ከተማ #በዛሬው_ዕለት በደረሰ #የትራፊክ_አደጋ የሰው ህይወት ማለፉ ተሰምቷል።
Via Gamo Zone Administration public Relation office
•ወገኖቼ መነጋገር አለብን! እንደወጣን እየቀረን ነው! በየቦታው በየከተማው በትራፊክ አደጋ ብዙ ዜጎቻችን እያለቁ ነው።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#አርባምንጭ
በአርባምንጭ ከተማ #በዛሬው_ዕለት በደረሰ #የትራፊክ_አደጋ የሰው ህይወት ማለፉ ተሰምቷል።
Via Gamo Zone Administration public Relation office
•ወገኖቼ መነጋገር አለብን! እንደወጣን እየቀረን ነው! በየቦታው በየከተማው በትራፊክ አደጋ ብዙ ዜጎቻችን እያለቁ ነው።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የባህር ዳር ዩኒቨርሲቲ #በአርክቴክቸር የትምህርት ዘርፍ ያስተማራቸውን ተማሪዎች #በዛሬው ዕለት #አስመርቋል።
@tsegabwolde @tikvahethiopia
@tsegabwolde @tikvahethiopia
አቶ ሙስጠፌ ተሸለሙ!
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን #በዛሬው ዕለት ለሶማሌ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ መሐመድና ለባልደረቦቻቸው ሽልማት አበርክታለች።
ዛሬ በጅግጅጋ በተካሄደው የኦሮሞና የሶማሌ የህዝብ ለህዝብ መድረክ ላይ የተገኙት የቤተክርስቲያኗ አባቶች ለአቶ ሙስጠፋና ለባልደረቦቻቸው የቤተክርስቲያኗን የክብር ካባ ሸልመዋቸዋል።
ቤተክርስቲያኗ ለአቶ ሙስጠፋና ለባልደረቦቻቸው ሽልማቱን ያበረከተችው በተለይ አዲሱ የክልሉ አስተዳደር ለሰላም ላላው ቁርጠኝነት እውቅና ለመስጠት እንደሆነ በቤተክርስቲያኗ የሶማሌ ክልል ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ መቃሪዎስ ገልጸዋል።
ባለፈው ዓመት በጂግጂጋና አካባቢው በተነሳው ረብሻ በርካታ አብያተ ክርስቲያንና የሃይማኖት አባቶች ጉዳት እንደደረሰባቸው ይታወሳል።
Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን #በዛሬው ዕለት ለሶማሌ ክልል ምክትል ርእሰ መስተዳድር አቶ ሙስጠፋ መሐመድና ለባልደረቦቻቸው ሽልማት አበርክታለች።
ዛሬ በጅግጅጋ በተካሄደው የኦሮሞና የሶማሌ የህዝብ ለህዝብ መድረክ ላይ የተገኙት የቤተክርስቲያኗ አባቶች ለአቶ ሙስጠፋና ለባልደረቦቻቸው የቤተክርስቲያኗን የክብር ካባ ሸልመዋቸዋል።
ቤተክርስቲያኗ ለአቶ ሙስጠፋና ለባልደረቦቻቸው ሽልማቱን ያበረከተችው በተለይ አዲሱ የክልሉ አስተዳደር ለሰላም ላላው ቁርጠኝነት እውቅና ለመስጠት እንደሆነ በቤተክርስቲያኗ የሶማሌ ክልል ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብጹዕ አቡነ መቃሪዎስ ገልጸዋል።
ባለፈው ዓመት በጂግጂጋና አካባቢው በተነሳው ረብሻ በርካታ አብያተ ክርስቲያንና የሃይማኖት አባቶች ጉዳት እንደደረሰባቸው ይታወሳል።
Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
TIKVAH-ETHIOPIA
#AddisAbaba በአዲስ አበባ ከአራት ዓመታት በኃላ ለመጀመሪያ ጊዜ የመሬት ሊዝ ጨረታ መውጣቱን ሪፖርተር ጋዜጣ ዘግቧል። የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከአራት ዓመት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ የመሬት ሊዝ ጨረታ ያወጣ ሲሆን ለጨረታ የቀረቡት ይዞታዎች መነሻ ዋጋ ከፍተኛው 2,213 ብር መሆኑ ታውቋል። የአዲሰ አበባ ከተማ አስተዳደር የመሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ዛሬ ግንቦት 7 ቀን 2015 ዓም…
#Update #የመሬት_ሊዝ_ጨረታ
" በ7 ክ/ከተሞች የመሬት ሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች ከአፍታ ቆይታ በኃላ ይለያሉ " - የአ/አ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ላለፉት አምስት ዓመታት ተቋርጦ የነበረውን የመሬት ሊዝ ጨረታ ዛሬ አስጀምሯል።
ይህንንም ተከትሎ ቢሮው በሁሉም ክፍለ ከተሞች 14 ነጥብ 13 ሄክታር መሬት በሊዝ ለማጫረት ማዘጋጀቱን ገልጿል።
በጨረታ የቀረበው መሬት አገራዊ ፋይዳ ላላቸው ለተለያዩ ዓላማዎች የሚውል ነው ተብሏል።
በአስራ አንዱ ክፍለ ከተሞች 24 ሺህ የጨረታ ሰነዶችን በማዘጋጀት ባለፋት አስር ቀናት 21 ሺህ 636 የሚሆኑት የጨረታ ሰነዶች መሸጥ መቻሉም ተጠቁሟል።
የመጀመሪያው ጨረታ #በዛሬው ዕለት በ7 ክፍለ ከተሞች ፦
👉 በቦሌ፣
👉 በንፋስ ስልክ ላፍቶ፣
👉 በልደታ፣
👉 በአዲስ ከተማ፣
👉 በቂርቆስ፣
👉 በጉለሌና በየካ ክፍለ ከተሞች ተጀምሯል።
በእነዚህ ክፍለ ከተሞች 2 ሺህ 852 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዶቻቸውን ወደ ጨረታ ሳጥኑ አስገብተዋል።
የጨረታ ሂደቱ አሁን በመካሄድ ላይ ሲሆን አሸናፊዎች ከአፍታ ቆይታ በኋላ የሚለዩ ይሆናል።
በቀጣዮች ቀናት የጨረታ ሒደቱ በሌሎች ክ/ከተሞች እንደሚቀጥል ታውቋል።
#ኢዜአ
@tikvahethiopia
" በ7 ክ/ከተሞች የመሬት ሊዝ ጨረታ አሸናፊዎች ከአፍታ ቆይታ በኃላ ይለያሉ " - የአ/አ መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር መሬት ልማትና አስተዳደር ቢሮ ላለፉት አምስት ዓመታት ተቋርጦ የነበረውን የመሬት ሊዝ ጨረታ ዛሬ አስጀምሯል።
ይህንንም ተከትሎ ቢሮው በሁሉም ክፍለ ከተሞች 14 ነጥብ 13 ሄክታር መሬት በሊዝ ለማጫረት ማዘጋጀቱን ገልጿል።
በጨረታ የቀረበው መሬት አገራዊ ፋይዳ ላላቸው ለተለያዩ ዓላማዎች የሚውል ነው ተብሏል።
በአስራ አንዱ ክፍለ ከተሞች 24 ሺህ የጨረታ ሰነዶችን በማዘጋጀት ባለፋት አስር ቀናት 21 ሺህ 636 የሚሆኑት የጨረታ ሰነዶች መሸጥ መቻሉም ተጠቁሟል።
የመጀመሪያው ጨረታ #በዛሬው ዕለት በ7 ክፍለ ከተሞች ፦
👉 በቦሌ፣
👉 በንፋስ ስልክ ላፍቶ፣
👉 በልደታ፣
👉 በአዲስ ከተማ፣
👉 በቂርቆስ፣
👉 በጉለሌና በየካ ክፍለ ከተሞች ተጀምሯል።
በእነዚህ ክፍለ ከተሞች 2 ሺህ 852 ተጫራቾች የጨረታ ሰነዶቻቸውን ወደ ጨረታ ሳጥኑ አስገብተዋል።
የጨረታ ሂደቱ አሁን በመካሄድ ላይ ሲሆን አሸናፊዎች ከአፍታ ቆይታ በኋላ የሚለዩ ይሆናል።
በቀጣዮች ቀናት የጨረታ ሒደቱ በሌሎች ክ/ከተሞች እንደሚቀጥል ታውቋል።
#ኢዜአ
@tikvahethiopia
👍883👎407❤104🕊42🙏27🥰17😢10😱8