TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
አሳዛኝ ዜና!

በሀድያ ዞን #ሾኔ ከተማ ዛሬ በደረሰ የተሽከርካሪ አደጋ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉን ፖሊስ አስታወቀ። አደጋው የደረሰው በከተማው ወርልድ ቪዥን በተባለው አካባቢ የተርጋ ቁጥሩ ኮድ 1-14316 ደ.ሕ  ባለሶስት እግር ባጃጅ ተሽከርካሪ ከሻሸመኔ ወደ ወላይታ ሶዶ ይጓዝ ከነበረ ኮድ 3-05477 ደ.ሕ ከሆነ የጭነት አይሱዙ ጋር በመጋጨቱ ነው፡፡

የሾኔ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ጽህፈት ቤት የትራፊክ ስራ ሂደት አስተባባሪ ዋና ሳጅን አዲሴ በርገኖ እንደገለጹት ባጃጁ መስመሩን ስቶ በፍጥነት በመጓዝ ላይ ከነበረው አይሱዙ የጭነት ተሽከርካሪው ጋር በመላተሙ አደጋው ሊደርስ ችሏል። በአደጋውም በባጃጁ ውስጥ የነበሩ አሽከርካሪውን ጨምሮ የአራት ሰዎች ህይወት ማለፉን አስታውቀዋል።

#የሟቾቹ አስክሬን ቤተሰቦች እንዲረከቡ መደረጉንም አመልክተው የአይሱዙ አሽከርካሪ ለጊዜው ቢሰወርም ፖሊስ በክትትል ላይ መሆኑን ገልጸዋል። ዋና ሳጅን አዲሴ የሰው ህይወትና ንብረትን ከጥፋት ለመታደግ አሽከርካሪዎች ርቀታቸውንና ፍጥነታቸውን  በመቆጣጠር ጥንቃቄ ማድረግ እንዳለባቸው አሳስበዋል፡፡

ምንጭ፦ ኢዜአ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#ሾኔ

በሀድያ ዞን ሾኔ ከተማ በህገ ወጥ መንገድ የምግብ ዘይት ፣ ስኳር እና ቡና አከማችተዋል የተባሉ ሶስት ግለሰቦች መያዙን ፖሊስ አስታወቀ፡፡ ንብረቱ  የተገኘው  ትናንት  በከተማዋ  በሚኖሩ የግለሰቦቹ  ቤቶች  ውስጥ ተከማችቶ ነው፡፡ ፖሊስ ከህብረተሰቡ በደረሰው ጥቆማ በቤቶች ባደረገው  ፍተሻ አንድ ሺህ ሰባት መቶ ሁለት ሊትር ዘይት፣ ሰባት ኩንታል ቡና እና ሶስት ኩንታል ስኳር ማግኘታቸውን የከተማዋ አስተዳደር  ፖሊስ አዛዥ ዋና ሳጅን ታረቀኝ ሶረቶ ገልጸዋል።

(ENA)

@tikvahethiopiabot @tikvahethiopia