TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
የመረጃ ሳጥኑ ወደ ፈረንሳይ ተልኳል‼️

ባሳለፍነው እሁድ #የተከሰከሰው የኢትዮጵያ አየር መንገድ ቦይንግ 737-8 ማክስ አውሮፕላን የበረራ መረጃ ሳጥንና የበረራ መቆጣጠሪያ ክፍል መቅረፀ ድምፅ ለምርመራ ወደ ፈረንሳይ መላኩ ተገለፀ።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እንዳስታወቀው፥ በአደጋ ምርመራ ቢሮ የሚመራ የኢትዮጵያ ቡድን የበረራ መረጃ ሳጥን እና የበረራ መቆጣጠሪያ ክፍል መቅረፀ ድምፅ በመያዝ ለቀጣይ ምርመራ ወደ ፓሪስ #ፈረንሳይ አቅንቷል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚው አቶ ተወልደ ገብረማርያም በትናንትናው እለት ከአሜሪካው ሲ.ኤን.ኤን የቴሌቪዥ ጣቢያ ጋር በነበራቸው ቆይታ ኢትዮጵያ የአውሮፕላኑ የመረጃ ሳጥን መመርመሪያ መሳሪያ ስለሌላት ለምርመራ ወደ ውጭ ይላካል ማለታቸው ይታወሳል።

አቶ ተወልደ፥ አውሮፕላኑ የበረራ መረጃ ሳጥንና የበረራ መቆጣጠሪያ ክፍል መቅረፀ ድምፅ ምርመራ ከቅርበትና ከፍጥነት አኳያ  ወደ አውሮፓ ሀገራት ሊላክም ይችላልም ብለው ነበር።

በዚህም መሰረት ነው የአደጋ ምርመራ ቢሮ የሚመራ የኢትዮጵያ ቡድን የበረራ መረጃ ሳጥን እና የበረራ መቆጣጠሪያ ክፍል መቅረፀ ድምፅ በመያዝ ለቀጣይ ምርመራ ወደ ፈረንሳይ ያቀናው።

ምንጭ፦ FBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
😱1
#update በኢትዮጵያ የአደጋ ምርመራ ቢሮ የተመራ ልዑካን ቡድን #የበረራ_መረጃ መመዝገበያ እና የአብራሪዎች ክፍል #የድምጽ_መቅጃ መሳሪያዎችን ይዞ ወደ #ፈረንሳይ_መዘጓዙን የኢትዮጵያ አየር መንገድ አስታውቋል።

@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደቡብ አፍሪካ የኮሮና ቫይረስ ስርጭትን ለመቆጣጠር የጉዞ እገዳ ያደረገችባቸው ሀገራት 9 ደርሰዋል። ሀገራቱ ፦ ቻይና ፣ ፈንሳይ ፣ ጀርመን ፣ ጣልያን ፣ ደቡብ ኮሪያ ፣ እንግሊዝ ፣ አሜሪካ ፣ ስፔን እና ኢራን ናቸው። ከዚህ ቀደም በእገዳው ውስጥ ያልተካተተችው #ፈረንሳይ እገዳው ተጥሎባታል።

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
ከዓለም ዙሪያ ፦

➡️ #አሜሪካ - በኒውዮርክ የተቃውሞ ሰልፍ ተካሂዷል። ሰልፉ በመሳሪያ የገዙ ጥቃቶችን ለማውገዝ የተካሄደ ነው። ሰልፉ የተካሄደው አንድ ወጣት በቴክሳስ ሮብ በሚሰኝ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት 19 ህፃናት ተማሪዎችን እና 2 መምህራንን በአሰቃቂ ሁኔታ ከገደለ ከቀናት በኃላ ነው።

➡️ #ስፔን - በሰሜናዊ ስፔን ላ ሪዮጃ ክልል በባዮዲዝል ማምረቻ ፋብሪካ ላይ በደረሰ ፍንዳታ ቢያንስ 2 ሰዎች መሞታቸው ሪፖርት ተደርጓል።

➡️ #የመን - በየመን አደን ከተማ ሰዎች በሚበዙበት በተጨናነቀ ገበያ ላይ በደረሰ ፍንዳታ በትንሹ 4 ሰዎች ሲሞቱ በርካቶች መቁሰላቸው ታውቋል፤ እስካሁን ለጥቃቱ ኃላፊነት ወስዳለሁ ብሎ ብቅ ያለ የለም።

➡️ #ሱዳን - ከወራት በፊት በሱዳን የተካሄደውም ወታደራዊ መፈንቅለ መንግስት ተከትሎ የተነሳው ተቃውሞ አሁንም ያልበረደ ሲሆን ትላንትና በሺዎች የሚቆጠሩ ተቃዋሚዎች በካርቱም ጎዳናዎች ላይ ተቃውሞ አሰምተዋል። የጥቅምቱ መፈንቅለ መንግስት ሀገሪቱን ወደ ፖለቲካዊ ቀውስ አስገብቷል።

➡️ #ጣልያን - የጣሊያን ጠቅላይ ሚኒስትር ማሪዮ ድራጊ የሩሲያው ፕሬዜዳንህ ፑቲን አሁን ላይ በዓለም የሚየው የምግብ ችግር "በሩሲያ ላይ የተጣለው ማዕቀብ ነው " ብለው እንደነገራቸው ተናግረዋል። የሩስያ እና ዩክሬን ጦርነት ከጀመረ አንስቶ ምዕራባውያን ሀገራት ሩስያ ላይ እጅግ ከፍተኛ የሚባሉ ማዕቀቦችን እየጣሉ እንደሆነ ይታወቃል። ለእነዚህ ማዕቀቦችም ሩስያ ምላሽ ከመስጠት ወደኃላ አላለችም።

➡️ #ቱርክ #ፈረንሳይ - የቱርክ ፕሬዜዳንት ሬሲፕ ጣይብ ኤርዶጋን ከፈረንሳይ ፕሬዜዳንት ኢማኑኤል ማክሮን የስውዲን እና ፊንላንድ ለNATO አባልነት ባቀረቡት ማመልከቻ፣ በዩክሬን ሩስያ ጦርነት፣ በቀጠናዊ ጉዳዮች እና በሌሎችም ጉዳዮች ላይ ተገናኝተው መክረዋል።

@tikvahethiopia
👍1😭1
#ይገምቱ

የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ማን ይሆናል ?

#ፈረንሳይ እና #አርጀንቲና ከ12:00 ጀምሮ የዓለም ዋንጫው ባለድል ለመሆን ከፍተኛ ፍልሚያ ያደርጋሉ።

የኳታሩን የዓለም ዋንጫ ማን ያሸንፋል ? የዋንጫው ባለቤት የሚሆነውን #ሀገር በትክክል ለመገመቱ 20 የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የ250 የሞባይል ብር ካርድ በሥጦታ የምናበረክት ይሆናል።

20 ትክክለኛ ገማቾች የሚለየቱ መልዕክቱን በላኩበት ቅደም ተከተል ነው።

ግምቱን መላክ ሚቻለው ጨዋታው እስከሚጀምርበት ደቂቃ ድረስ ብቻ ሲሆን #Edit የተደረገ ምላሽ ተቀባይነት አይኖረም።

(ግምትዎን #ከታች_ባለው የአስተያየት ማስቀመጫ ላይ ያኑሩ ፤ ፈረንሳይ ወይስ አርጀንቲና ? ከሁለቱ ሀገራት አንዱን ብቻ ይምረጡ ፤ ውጤት / በቁጥር መገመት #አያስፈልግም )

@tikvahethiopia
👍1.42K184🕊102👎101🙏82🥰62😱42😢13
TIKVAH-ETHIOPIA
#ይገምቱ የዓለም ዋንጫ አሸናፊ ማን ይሆናል ? #ፈረንሳይ እና #አርጀንቲና ከ12:00 ጀምሮ የዓለም ዋንጫው ባለድል ለመሆን ከፍተኛ ፍልሚያ ያደርጋሉ። የኳታሩን የዓለም ዋንጫ ማን ያሸንፋል ? የዋንጫው ባለቤት የሚሆነውን #ሀገር በትክክል ለመገመቱ 20 የቲክቫህ ቤተሰብ አባላት የ250 የሞባይል ብር ካርድ በሥጦታ የምናበረክት ይሆናል። 20 ትክክለኛ ገማቾች የሚለየቱ መልዕክቱን በላኩበት ቅደም ተከተል…
#Update #WorldCup

በFIFA የዓለም ሀገራት ዋንጫ የፍፃሜ ጨዋታ እያደረጉ የሚገኙት #ፈረንሳይ እና #አርጀንቲና መደበኛ 90 ደቂቃውን በ2 ለ 2 በሆነ ውጤት አጠናቀዋል።

ምንም እንኳን አርጀንቲና በሜሲ እና ዲማሪያ ጎል የመጀመሪያውን አጋማሽ በበላይነት ብታጠናቅቅም ፈረንሳይ በሁለተኛው አጋማሽ ቡድኗን አጠናክራው በወጣቱ ምባፔ ሁለት ጎሎች አቻ መሆን ችላለች።

ጨዋታው አቻ መሆኑን ተከትሎ ወደ ተጨማሪ 30 ደቂቃ አምርቷል።

ይህን የዓለም ሀገራት የእግር ኳስ ዋንጫ ፍልሚያ ሚሊዮኖች እየተከታተሉት ይገኛሉ። ማን አሸናፊ ይሆን ?

More : https://tttttt.me/tikvahethsport

@tikvahethiopia
👍863😢10266🥰54😱37👎33🕊29🙏14