TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update ሱማሌ ክልል⬇️

አቶ #ሙስጠፋ_ሞሐመድ_ዑመር ጊዜያዊ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት ሆነው ተሾሙ።

አቶ ሙሰጠፋ ሞሐመድ የክልሉ ጊዜያዊ ፕሬዚዳንት ሆነው እንዲመሩ የሶማሌ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ሶህዴፓ) የሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴው እንደመረጣቸው አዲስ አበባ የሚገኘው የቢቢሲ ሶማልኛ ሪፖርተር #አረጋግጧል

አቶ ሙሰጠፋ ሞሐመድ የክልሉ ጊዜያዊ ፕሬዚዳንትነታቸው በተጨማሪ የሶህዴፓ ምክትል ሊቀመንበር ተደርገው ተሹመዋል።

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጸ/ቤት ኃላፊ ሚንስትሩ አህመድ ሺዴ የሶህዴፓ ሊቀመንበር ተደርገው መሾማቸው ይታወሳል።

አቶ ሙስጠፋ የቀድሞ ፕሬዚዳንት አብዲ ሙሐመድ ኡመር የተለያዩ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶችን ይፈጽማሉ በማለት በተደጋጋሚ በመተቸት ይታወቃሉ።

የቀድሞ የኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል ፕሬዚዳንት የነበሩት አቶ አብዲ ሞሐመድ ኡመር ከስልጣናቸው ከተነሱ ሁለት ሳምንታት አልፈዋል።

አቶ አብዲ ሞሐመድ ክልል ፕሬዚዳንትነታቸው መነሳታቸው ከተሰማ ከሁለት ቀናት በኋላ አህመድ አብዲ ሼክ ሞሃመድ (ኤልካስ) ፕሬዚዳንት ተደርገው ተሹመው ነበር።

©BBC
@tsegabwolde @tikvahethiopia
👍1
#update ጅንካ⬇️

የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን በ60 ሚሊየን ብር ወጪ በጅንካ ከተማ ያስገነባው የከረጢት ፋብሪካ የምርት ስራው #ቆሟል

5 የኦሞ ኩራዝ ስኳር ፕሮጀክቶች በደቡብ ኦሞ ዞን መገንባታቸውን ተከትሎ በጂንካ ከተማ በ18 ነጥብ 2 ሄክታር መሬት ላይ ያረፈው የከረጢት ፋብሪካው "ኮርፖሬት ኒው ቢዝነስ ዴቨሎፕመንት” በተሰኘ ተቋም ግንባታው ተጠናቆ የሙከራ ምርት ማምረት ችሎ ነበር።

ሆኖም ፋብሪካውን የሚያስተዳድረው የብረታ ብረትና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን አምርቶ መሸጥ ለሚችል 3ኛ ወገን ሳያስተላልፍ በመቆየቱና ለሙከራ የቀረበው ግብዓትም በማለቁ አሁን ፋብሪካው ምርት ማቆሙን fbc በስፍራው ባደረገው ቅኝት #አረጋግጧል

የጅንካ ከረጢት ፋብሪካ በሙከራ ወቅት ከ400 ሺህ በላይ ከረጢት ያመረተ ሲሆን፥ ፍብሪካው ለሚመለከተው አካል አለመተላለፉን ተከትሎ የገበያ ትስስር ሊፈጠርለት አልቻለም።

ከዚህ ባሻገርም ፋብሪካው በራሱ በብረታ ብረት እና ኢንጂነሪንግ ኮርፖሬሽን የውስጥ ስምምነት መሰረት 130 ሰራተኞችን ቀጥሮ እንዲንቀሳቀስ ሲያደርግ ቢቆይም፤ በተጠቀሱት ምክንያቶች ስራ እንዲያቆም ሲደረግ 89 ሰራተኞች ከስራ እንዲሰናበቱ መደረጉ እና በበረሃ አበል ክፍያ ላይ ችግሮች መኖራቸው ቅሬታ እንዲፈጠር አድርጓል።

የጅንካ ከረጢት ፋብሪካ ዋና ስራ አስኪያጅ ሺህ አለቃ ቀረብህ ህብስቱ እንደተናገሩት፤ ፋብሪካውን ተረክቦ ምርት እያመረተ መሸጥ ለሚችል አካል ለማስተላለፍ እና የሙከራ ምርቶቹንም ለመሸጥ የጨረታ ማስታወቂያ ወጥቶ ክትትል እየተደረገ ነው።

የፋብሪካው የሰው ሃይል አስተዳደር አና ልማት ሃላፊው ሺህ አለቃ ማጆር ተሰማ በበኩላቸው ከስራ ገበታቸው የተሰናበቱ ሰራተኞች ፍብሪካው እስኪተላለፍ ድረስም ቢሆን እንዲመለሱ እና የክፍያ ቅሬታቸውም ውይይት እንዲደረግበት መወሰኑን ገልፀዋል።

የጅንካ ከረጢት ፋብሪካ በሙሉ አቅሙ መስራት ሲጀምር በአመት 30 ሚሊየን ከረጢት የማምረት አቅም ያለው ሲሆን በሙከራ ወቅት በቀን ከ1 መቶ ሺህ በላይ ከረጢት የማምረት ብቃት እንዳለው ተረጋግጧል።

ምንጭ፦ ፋና ብሮድካስቲንግ
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#update የደምቢ ዶሎ ዩኒቨርስቲ ፕሬዝዳንት ዶ/ር #ደላሳ_ቡልቻ ትናንት ባልታወቁ ታጣቂዎች ታፍነው መወሰዳቸውን የኦሮሚያ ክልል ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ጽህፈት ቤት #አረጋግጧል፡፡ የጽህፈት ቤቱ ምክትል ሃላፊ ደሬሳ ተረፈ ዛሬ ለDW እንደተናገሩት ሰውዬው ከእነ ሹፌራቸው የታፈኑት ሃዋ ጋላን ወረዳ፣ #በጋባ_ሮቢ በተባለች ከተማ ነው፡፡ ስለ አፋኞቹ ማንነት ተጠይቀው በአካባቢው ትጥቅ ትግል እንካሂዳለን የሚሉ ቡድኖች መኖራቸውን ጠቅሰው ማንነታቸው ግን ገና እየተጣራ ነው ብለዋል፡፡

Via~wazemaradio
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#Telegram

ከ10:20 ጀምሮ ቴሌግራም ተቋርጦ እንደነበረ ተጠቃሚዎች ገልፀዋል።

ችግሩ ሀገራችን ኢትዮጵያን ጨምሮ በተለያዩ አውሮፓ ሀገራት እና የመካከለኛው ምስራቅ ሀገራት ውስጥ ነው የተከሰተው።

ድርጅቱ ከተጠቀሰው ሰዓት አንስቶ ተጠቃሚዎች አገልግሎት ማግኘት እንዳልቻሉ #አረጋግጧል ፤ የችግሩን ምክንያት ግን አላሳወቀም።

በአሁን ሰዓት የቴሌግራም አገልግሎት ተቋርጦ በነበረባቸው ሁሉም ቦታዎች ላይ መስራት ጀምሯል ፤ ድርጅቱም ይህንን አሳውቋል።

@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia