የከፋ ዞን ምክር ቤት‼️
የካፋ ዞን ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ #ቦንጋ ላይ የተገነባው ብሔራዊ የቡና ሙዚዬም ሥራ እንዲጀምር ወሰነ።
የካፋ ዞን #የክልልነት ጥያቄንም በምክር ቤቱ አባላት ጸድቋል።
የዞኑ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ አቶ ግርማ ወልደ ሚካዔል ለኢዜአ እንደገለጹት ጉባዔው በዛሬው ወሎ በሁለት አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አስተሏልፏል ።
ጉባዔው ውሳኔ ካሳለፈባቸው አጀንዳዎች አንዱ በዞኑ ቦንጋ ከተማ ተገንብቶ ለአመታት ሥራ ያልጀመረው ሙዚዬም ወደ ሥራ እንዲገባ ወስኗል።
“ከምሁራን የተውጣጣ ኮሚቴ ተቋቁሞ ከሚመለከተው አካል ጋር በመነጋገር ሙዚዬሙ ወደ ሥራ እንዲገባ ውሳኔ ተላልፏል” ብለዋል ።
የካፋ ሕዝብ የክልልነት ጥያቄ ለምክር ቤቱ ቀርቦ በአባላቱ ውይይት ከተደረገበት በኋላ በሙሉ ድምጽ መፅደቁን ምክትል አፈ ጉባዔው ተናግረዋል።
ጉባኤው ነገ የዞኑን የ2010 በጀት ዓመት የአስፈጻሚ አካላት የሥራ ክንውን በመገምገምና በቀጣይ ዕቅድ ላይ በመወያየት ውሳኔ እንደሚያሳልፍ አመላክተዋል ።
እንደ ምክትል አፈ ጉባኤው ገለጻ በተለያዩ ምክንያቶች ያልጸደቀውን የዞኑን የ2011 በጀትና የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ሹመትም እንደሚፀድቅ ይጠበቃል።
ምንጭ፦ ena
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የካፋ ዞን ምክር ቤት አምስተኛ ዓመት 11ኛ መደበኛ ጉባዔ #ቦንጋ ላይ የተገነባው ብሔራዊ የቡና ሙዚዬም ሥራ እንዲጀምር ወሰነ።
የካፋ ዞን #የክልልነት ጥያቄንም በምክር ቤቱ አባላት ጸድቋል።
የዞኑ ምክር ቤት ምክትል አፈ ጉባዔ አቶ ግርማ ወልደ ሚካዔል ለኢዜአ እንደገለጹት ጉባዔው በዛሬው ወሎ በሁለት አጀንዳዎች ላይ ውሳኔ አስተሏልፏል ።
ጉባዔው ውሳኔ ካሳለፈባቸው አጀንዳዎች አንዱ በዞኑ ቦንጋ ከተማ ተገንብቶ ለአመታት ሥራ ያልጀመረው ሙዚዬም ወደ ሥራ እንዲገባ ወስኗል።
“ከምሁራን የተውጣጣ ኮሚቴ ተቋቁሞ ከሚመለከተው አካል ጋር በመነጋገር ሙዚዬሙ ወደ ሥራ እንዲገባ ውሳኔ ተላልፏል” ብለዋል ።
የካፋ ሕዝብ የክልልነት ጥያቄ ለምክር ቤቱ ቀርቦ በአባላቱ ውይይት ከተደረገበት በኋላ በሙሉ ድምጽ መፅደቁን ምክትል አፈ ጉባዔው ተናግረዋል።
ጉባኤው ነገ የዞኑን የ2010 በጀት ዓመት የአስፈጻሚ አካላት የሥራ ክንውን በመገምገምና በቀጣይ ዕቅድ ላይ በመወያየት ውሳኔ እንደሚያሳልፍ አመላክተዋል ።
እንደ ምክትል አፈ ጉባኤው ገለጻ በተለያዩ ምክንያቶች ያልጸደቀውን የዞኑን የ2011 በጀትና የዞኑ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ሹመትም እንደሚፀድቅ ይጠበቃል።
ምንጭ፦ ena
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ደኢህዴን‼️
በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ባሉ አንዳንድ የዞን ም/ቤቶች የሚነሱ #የክልልነት_ጥያቄዎች ከደኢህዴን ጉባኤ አቅጣጫ ውጭ መሆናቸውን የድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡
ማዕከላዊ ኮሚቴው ይህን ያስታወቀው በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ መሆኑን የማዕከላዊ ኮሚቴው ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡
ኃላፊው እንዳሉት ማዕከላዊ ኮሚቴው የህብረተሰቡን ጥያቄዎች ለመመለስ በ10ኛው የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባኤ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን አፈፃፀም ሂደት ገምግሟል፡፡
አስተዳደራዊ አደረጃጀትን በተመለከተ ዝርዝር ጥናት እየተደረገ መሆኑን የጠቀሰው ማዕከላዊ ኮሚቴው ጥናቱ ሲጠናቀቅ በጉባኤው የፀደቁ አዳዲስ የመዋቅር አደረጃጀቶች በክልሉ ም/ቤት ህጋዊ ማዕቀፍ ኖሯቸው እንደሚቋቋሙ ገልጿል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በክልሉ እየተበራከቱ የመጡትን የክልላዊ አደረጃጀት ጥያቄዎች በተመለከተም ጥልቅ ጥናት የሚያደርግ ከባለሙያዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጣ ቡድን መቋቋሙ ተገልጿል፡፡
ጥናቱን ተከትሎም ተገቢው ምላሽ እንደሚሰጥና ከዚህ ውጭ በዞን ም/ቤቶችና በተለያየ መልኩ የሚነሱ ጥያቄዎች ከድርጅቱ ጉባኤ አቅጣጫ ውጭ መሆናቸውን ማዕከላዊ ኮሚቴው አስታውቋል፡፡
ተቋማትን በመዝጋትና የዜጎችን ነፃ እንቅስቃሴ በመገደብ ሃሳብን በኃይል ለመጫን የሚደረጉ ተግባራት ተቀባይነት የላቸውም ያለው ኮሚቴው የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ግልፅ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
ማዕከላዊ ኮሚቴው የኅብረተሰቡን ጥያቄዎች ተከትሎ በተከሰቱ ግጭቶች በደረሰው የህይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘንም መግለፁን የማዕከላዊ ኮሚቴው ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
በደቡብ ብሔር ብሔረሰቦችና ሕዝቦች ክልል ባሉ አንዳንድ የዞን ም/ቤቶች የሚነሱ #የክልልነት_ጥያቄዎች ከደኢህዴን ጉባኤ አቅጣጫ ውጭ መሆናቸውን የድርጅቱ ማዕከላዊ ኮሚቴ አስታወቀ፡፡
ማዕከላዊ ኮሚቴው ይህን ያስታወቀው በክልሉ ወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ዛሬ ባካሄደው አስቸኳይ ስብሰባ መሆኑን የማዕከላዊ ኮሚቴው ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡
ኃላፊው እንዳሉት ማዕከላዊ ኮሚቴው የህብረተሰቡን ጥያቄዎች ለመመለስ በ10ኛው የደኢህዴን ድርጅታዊ ጉባኤ የተቀመጡ አቅጣጫዎችን አፈፃፀም ሂደት ገምግሟል፡፡
አስተዳደራዊ አደረጃጀትን በተመለከተ ዝርዝር ጥናት እየተደረገ መሆኑን የጠቀሰው ማዕከላዊ ኮሚቴው ጥናቱ ሲጠናቀቅ በጉባኤው የፀደቁ አዳዲስ የመዋቅር አደረጃጀቶች በክልሉ ም/ቤት ህጋዊ ማዕቀፍ ኖሯቸው እንደሚቋቋሙ ገልጿል፡፡
ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በክልሉ እየተበራከቱ የመጡትን የክልላዊ አደረጃጀት ጥያቄዎች በተመለከተም ጥልቅ ጥናት የሚያደርግ ከባለሙያዎች፣ ምሁራንና የተለያዩ የኅብረተሰብ ክፍሎች የተውጣጣ ቡድን መቋቋሙ ተገልጿል፡፡
ጥናቱን ተከትሎም ተገቢው ምላሽ እንደሚሰጥና ከዚህ ውጭ በዞን ም/ቤቶችና በተለያየ መልኩ የሚነሱ ጥያቄዎች ከድርጅቱ ጉባኤ አቅጣጫ ውጭ መሆናቸውን ማዕከላዊ ኮሚቴው አስታውቋል፡፡
ተቋማትን በመዝጋትና የዜጎችን ነፃ እንቅስቃሴ በመገደብ ሃሳብን በኃይል ለመጫን የሚደረጉ ተግባራት ተቀባይነት የላቸውም ያለው ኮሚቴው የህግ የበላይነትን የማረጋገጥ ስራ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ግልፅ አቅጣጫ አስቀምጧል፡፡
ማዕከላዊ ኮሚቴው የኅብረተሰቡን ጥያቄዎች ተከትሎ በተከሰቱ ግጭቶች በደረሰው የህይወት መጥፋትና የአካል ጉዳት የተሰማውን ጥልቅ ሃዘንም መግለፁን የማዕከላዊ ኮሚቴው ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሞገስ ባልቻ ተናግረዋል፡፡
ምንጭ፦ etv
@tsegabwolde @tikvahethiopia
#NewsAlert
"ለሲዳማ የክልልነት ጥያቄ የምርጫ ቦርድን ስራ በትእግስት መጠባበቅ ይገባል'" አቶ ቃሬ ጫዌቻ
.
.
#የክልልነት ጥያቄው በህገ-መንግስቱ መሰረት ምላሽ እንዲያገኝ የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ስራ በመጀመሩ መላው የሲዳማ ብሔር ተወላጆች በትዕግስት እንዲጠባበቁ የሲዳማ ዞን አስተዳዳሪ አስታወቁ።
ዋና አስተዳዳሪው አቶ ቃሬ ጫዊቻ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በሲዳማ የክልልነት ጥያቄ ዙሪያ ህዝበ ውሳኔ ለማድረግ እንዲቻል ቅድመ-ዝግጅቱን ጀምሯል።
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ትናንት በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው ህዝበ ውሳኔውን ለማድረግ እንዲያስችል በደቡብ ክልልና በሲዳማ ዞን መከናወን ያለባቸውን ተግባራት በመለየት ማሳወቁንና እስከ ሐምሌ 19 ድረስ ዝርዝሩን በጽሁፍ ማቅረብ እንዲቻል የጊዜ ገደብ መስጠቱን አስታውቀዋል።
የሲዳማ ዞን አስተዳደር ከክልሉ መንግስትና ከደኢህዴን ጋር በመሆን በጥያቄው ዙሪያ በጋራ እየሰሩ እንደሚገኙና ምርጫ ቦርድ በአምስት ወራት ጊዜ ውስጥ ህዝበ ውሳኔ እንደሚደረግ በመግለጹ መላው የሲዳማ ተወላጆችና ወጣቶች ጉዳዩን በትዕግስት እንዲጠብቁ አሳስበዋል።
ቦርዱ በህዝበ ውሳኔ ማደራጀት ዙሪያ ከሲዳማ ዞንና ከክልሉ መንግስት ጋር በተለያዩ ጊዜያት መወያየቱን ያስታወሱት አቶ ቃሬ ህዝበ ውሳኔውን አምስት ወር ባልሞላ ጊዜ አደራጅቶ ለጥያቄው አፋጣኝ ምላሽ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።
Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia
"ለሲዳማ የክልልነት ጥያቄ የምርጫ ቦርድን ስራ በትእግስት መጠባበቅ ይገባል'" አቶ ቃሬ ጫዌቻ
.
.
#የክልልነት ጥያቄው በህገ-መንግስቱ መሰረት ምላሽ እንዲያገኝ የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ስራ በመጀመሩ መላው የሲዳማ ብሔር ተወላጆች በትዕግስት እንዲጠባበቁ የሲዳማ ዞን አስተዳዳሪ አስታወቁ።
ዋና አስተዳዳሪው አቶ ቃሬ ጫዊቻ ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ እንዳሉት ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ በሲዳማ የክልልነት ጥያቄ ዙሪያ ህዝበ ውሳኔ ለማድረግ እንዲቻል ቅድመ-ዝግጅቱን ጀምሯል።
ብሄራዊ ምርጫ ቦርድ ትናንት በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው ህዝበ ውሳኔውን ለማድረግ እንዲያስችል በደቡብ ክልልና በሲዳማ ዞን መከናወን ያለባቸውን ተግባራት በመለየት ማሳወቁንና እስከ ሐምሌ 19 ድረስ ዝርዝሩን በጽሁፍ ማቅረብ እንዲቻል የጊዜ ገደብ መስጠቱን አስታውቀዋል።
የሲዳማ ዞን አስተዳደር ከክልሉ መንግስትና ከደኢህዴን ጋር በመሆን በጥያቄው ዙሪያ በጋራ እየሰሩ እንደሚገኙና ምርጫ ቦርድ በአምስት ወራት ጊዜ ውስጥ ህዝበ ውሳኔ እንደሚደረግ በመግለጹ መላው የሲዳማ ተወላጆችና ወጣቶች ጉዳዩን በትዕግስት እንዲጠብቁ አሳስበዋል።
ቦርዱ በህዝበ ውሳኔ ማደራጀት ዙሪያ ከሲዳማ ዞንና ከክልሉ መንግስት ጋር በተለያዩ ጊዜያት መወያየቱን ያስታወሱት አቶ ቃሬ ህዝበ ውሳኔውን አምስት ወር ባልሞላ ጊዜ አደራጅቶ ለጥያቄው አፋጣኝ ምላሽ እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።
Via #ENA
@tsegabwolde @tikvahethiopia