TIKVAH-ETHIOPIA
#Update ፍርድ ቤት በዋስ ከእስር እንዲፈቱ የወሰነላቸው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ ጋዜጠኛ መዓዛ መሀመድ እና ጋዜጠኛ ሰለሞን ሹምዬ ከእስር አልተለቀቁም። ዛሬ ግንቦት 30 ቀን 2014 ዓ.ም የፌደራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት በዋለው ችሎት፣ 3ቱ ጋዜጠኖች በ10 ሺ ብር ዋስ እንዲለቀቁ መወሰኑ ይታወሳል። ነገር ግን መርማሪ ፖሊስ ይግባኝ ለማለት ለ8 ሰዓት ቀጥሮ ነበር ሆኖም ችሎቱን የሚመሩት…
#ችሎት
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ መዓዛ መሐመድ እና ሰለሞን ሹምዬ ላይ የቀረበውን ይግባኝ መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለነገ ሐሙስ ሰኔ 2/2014 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በዛሬው ችሎት፤ ለ3ቱ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በስር ፍርድ ቤት የተፈቀደው ዋስትና ውድቅ እንዲደረግ እና 14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
የቀረበውን ይግባኝ መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለነገ ሐሙስ ሰኔ 2/2014 ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
@tikvahethiopia
የፌደራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ፣ መዓዛ መሐመድ እና ሰለሞን ሹምዬ ላይ የቀረበውን ይግባኝ መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለነገ ሐሙስ ሰኔ 2/2014 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።
የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በዛሬው ችሎት፤ ለ3ቱ የመገናኛ ብዙሃን ባለሙያዎች በስር ፍርድ ቤት የተፈቀደው ዋስትና ውድቅ እንዲደረግ እና 14 ቀናት ተጨማሪ የምርመራ ጊዜ እንዲፈቀድለት ፍርድ ቤቱን ጠይቋል።
የቀረበውን ይግባኝ መርምሮ ትዕዛዝ ለመስጠት ለነገ ሐሙስ ሰኔ 2/2014 ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ኢትዮጵያ ኢንሳይደር ዘግቧል።
@tikvahethiopia
👍1😢1
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update #ችሎት የአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ዛሬ ግንቦት 22/2014 ዓ/ም በዋለው ችሎት የብርጋዴል ጀኔራል ተፈራ ማሞን ጉዳይ ተመልክቷል። የመርማሪ ቡድኑ ምርመራዬን ስላልጨረስኩ የተለያዩ ማስረጃዎችን ከባንክ፣ ከብሔራዊ መረጃና ደህንነት፣ ከኢሳት እና ከሌሎች ተቋማት የምንሰበስባቸው መረጃዎች ስላሉ የ14 ቀናት ተጨማሪ የጊዜ ቀጠሮ እንዲሰጠው ጠይቋል። የተከሳሽ ጠበቃ በበኩላቸው አስፈላጊ ናቸው…
#Update #ችሎት #ብርጋዴር_ጄነረል_ተፈራ_ማሞ
የአብክመ ጠቅላይ ፍ/ቤት ዛሬ ሰኔ 2 ቀን 2014 ዓ/ም በዋለው ችሎት የብርጋዴል ጀኔራል ተፈራ ማሞን ጉዳይ ተመልክቷል።
በዚህም ፤ የጊዜ ቀጠሮውን ጉዳይ መርማሪ ፖሊስ ምርመራየን ጨርሸ የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቢ ህግ ለመላክ በዝግጅት ላይ ነኝ ያለ ሲሆን የክልል ዐቃቤ ህግ በችሎት ቀርቦ አዎ ምርመራው አልቋል የክስ መመስረቻ ጊዜ 15 ቀናት ይሰጠኝ ሲል ጠይቋል።
የተከሳሽ ጠበቃ በበኩላቸው ምርመራ ካለቀ ደንበኛችን የተከሰሱበት ጉዳይ ዋስትና የሚያስከለክል ባለመሆኑ እና ተጠርጣሪው ደንበኛችን ታዋቂ ሠው በመሆናቸው ሊጠፉ ስለማይችሉ የደንበኛችን የዋስትና መብት ይከበርላቸው ሲሉ ተከራክረዋል።
ፍርድ ቤቱም ሲሰጥ የነበረው የጊዜ ቀጠሮ ምርመራው ያለቀ በመሆኑ የጊዜ ቀጠሮውን ጉዳይ ዘግቷል።
በመቀጠል የተጠርጣሪ ጠበቆች ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ዐቃቤ ህግ አስተያየት እንዲሰጥበት አድርጓል።
ዐቃቤ ህግ በበኩሉ የተከሰሱበት ጉዳይ የሽብር ወንጀል ስለሆነ በተጨማሪም ከሚዲያ ጋር በተያያዙ ሌሎች ተጨማሪ ክሶች ሊቀርቡ ስለሚችሉ ዋስትና ሊፈቀድላቸው አይገባም ሲል ተከራክሯል።
ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶ የተጠርጣሪ የዋስትና ጥያቄ ላይ ብይን ለመስጠት ለነገ ለሰኔ 3/2014 ዓ/ም ቀጠሮ ሰጥቷል።
መረጃው የአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ነው።
@tikvahethiopia
የአብክመ ጠቅላይ ፍ/ቤት ዛሬ ሰኔ 2 ቀን 2014 ዓ/ም በዋለው ችሎት የብርጋዴል ጀኔራል ተፈራ ማሞን ጉዳይ ተመልክቷል።
በዚህም ፤ የጊዜ ቀጠሮውን ጉዳይ መርማሪ ፖሊስ ምርመራየን ጨርሸ የምርመራ መዝገቡን ለዐቃቢ ህግ ለመላክ በዝግጅት ላይ ነኝ ያለ ሲሆን የክልል ዐቃቤ ህግ በችሎት ቀርቦ አዎ ምርመራው አልቋል የክስ መመስረቻ ጊዜ 15 ቀናት ይሰጠኝ ሲል ጠይቋል።
የተከሳሽ ጠበቃ በበኩላቸው ምርመራ ካለቀ ደንበኛችን የተከሰሱበት ጉዳይ ዋስትና የሚያስከለክል ባለመሆኑ እና ተጠርጣሪው ደንበኛችን ታዋቂ ሠው በመሆናቸው ሊጠፉ ስለማይችሉ የደንበኛችን የዋስትና መብት ይከበርላቸው ሲሉ ተከራክረዋል።
ፍርድ ቤቱም ሲሰጥ የነበረው የጊዜ ቀጠሮ ምርመራው ያለቀ በመሆኑ የጊዜ ቀጠሮውን ጉዳይ ዘግቷል።
በመቀጠል የተጠርጣሪ ጠበቆች ባቀረቡት የዋስትና ጥያቄ ላይ ዐቃቤ ህግ አስተያየት እንዲሰጥበት አድርጓል።
ዐቃቤ ህግ በበኩሉ የተከሰሱበት ጉዳይ የሽብር ወንጀል ስለሆነ በተጨማሪም ከሚዲያ ጋር በተያያዙ ሌሎች ተጨማሪ ክሶች ሊቀርቡ ስለሚችሉ ዋስትና ሊፈቀድላቸው አይገባም ሲል ተከራክሯል።
ፍርድ ቤቱ የግራ ቀኙን ክርክር ሰምቶ የተጠርጣሪ የዋስትና ጥያቄ ላይ ብይን ለመስጠት ለነገ ለሰኔ 3/2014 ዓ/ም ቀጠሮ ሰጥቷል።
መረጃው የአብክመ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ነው።
@tikvahethiopia
👍3😢1