TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ስውዲን እና ፊንላንድን የNATO አባል የማድረጉ ሂደት 'በፍጥነት' ይካሄዳል ብለን እንጠብቃለን " - የNATO ዋና ጸሐፊ ጄንስ ስቶለተንበርግ ከሩስያ ጋር 1300 ኪሎ ሜትር የሚረዝም ድንበር የምትጋራው ፊንላንድ NATOን ለመቀላቀል የአባልነት ጥያቄዋን የፊታችን እሁድ ይፋ ታደርጋለች ተብሎ ይጠበቃል። ስውዲንም የአባልነት ጥያቄዋን በተመሳሳይ ቀን ታቀርባለች ተብሎ ነው የሚጠበቀው።…
#Update
የዩክሬን እና የፊንላንድ ፕሬዜዳንቶች በስልክ ተነጋገሩ።
በዋነኝነት NATOን ለመቀላቀል ባሳየችው ፍላጎት ሳቢያ ከሩስያ ጋር ዛሬም ድረስ መፍትሄ ያላገኘ አስከፊ ጦርነት ውስጥ የገባቸው #ዩክሬን እና NATOን ለመቀላቀል ጥያቄ ለማቅረብ ዝግጅት ላይ የምትገኘው #ፊንላንድ ፕሬዜዳንቶች በስልክ ተነጋግረዋል።
የፊንላዱ ፕሬዜዳንት ሳውሊ ኒኒስቶ፤ ከፕሬዜዳንት ቮልድሚር ዜሌንስኪ ጋር በነበራቸው ውይይት ሀገራቸው ለዩክሬን ያላትን ፅኑ ድጋፍ በድጋሜ እንዳረጋገጡላቸው ገልፀዋል።
ፕሬዜዳንቱ ፊንላንድ የNATO አባል ለመሆን እየሄደችበት ስላለው ሂደት እንዳሳወቋቸው ገልፀው የዩክሬኑ ፕሬዜዳንትም ያላቸውን ድጋፍ እንደገለፁለቸው በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ፅፈዋል።
የዩክሬን ፕሬዜዳንት ዜሌንስኪ በበኩላቸው ከፊንላዱ ፕሬዜዳንት ጋር በነበራቸው የስልክ ውይይት ፊንላንድ ለNATO አባልነት ለማመልከት ያላትን ዝግጁነት አድንቀው አመስግነዋል ፤ በተጨማሪ ስለ ዩክሬን የአውሮፓ ውህደት በተመለከተ መነጋገራቸውን አሳውቀዋል።
@tikvahethiopia
የዩክሬን እና የፊንላንድ ፕሬዜዳንቶች በስልክ ተነጋገሩ።
በዋነኝነት NATOን ለመቀላቀል ባሳየችው ፍላጎት ሳቢያ ከሩስያ ጋር ዛሬም ድረስ መፍትሄ ያላገኘ አስከፊ ጦርነት ውስጥ የገባቸው #ዩክሬን እና NATOን ለመቀላቀል ጥያቄ ለማቅረብ ዝግጅት ላይ የምትገኘው #ፊንላንድ ፕሬዜዳንቶች በስልክ ተነጋግረዋል።
የፊንላዱ ፕሬዜዳንት ሳውሊ ኒኒስቶ፤ ከፕሬዜዳንት ቮልድሚር ዜሌንስኪ ጋር በነበራቸው ውይይት ሀገራቸው ለዩክሬን ያላትን ፅኑ ድጋፍ በድጋሜ እንዳረጋገጡላቸው ገልፀዋል።
ፕሬዜዳንቱ ፊንላንድ የNATO አባል ለመሆን እየሄደችበት ስላለው ሂደት እንዳሳወቋቸው ገልፀው የዩክሬኑ ፕሬዜዳንትም ያላቸውን ድጋፍ እንደገለፁለቸው በማህበራዊ ትስስር ገፃቸው ላይ ፅፈዋል።
የዩክሬን ፕሬዜዳንት ዜሌንስኪ በበኩላቸው ከፊንላዱ ፕሬዜዳንት ጋር በነበራቸው የስልክ ውይይት ፊንላንድ ለNATO አባልነት ለማመልከት ያላትን ዝግጁነት አድንቀው አመስግነዋል ፤ በተጨማሪ ስለ ዩክሬን የአውሮፓ ውህደት በተመለከተ መነጋገራቸውን አሳውቀዋል።
@tikvahethiopia
👍1