TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#update የአዲስ አበባ ፖሊስ አስጠነቀቀ⬇️

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በከተማዋ ሚስማር የተተከለበትን ዱላ የያዘ አንድም ሰው #እንዳልመለከት ብሏል፡፡

ምክትል ኮሚሽነር ዘላለም መንግስቴ በመዲናዋ የተከሰተውን አለመግባባት በተመለከተ ከሚመለከታቸው ጋር እየሰራሁ ነው ሲሉ ገልፀዋል፡፡

በህዝብ መገልገያ ንብረት፣ በመናፈሻዎች፣ በግንቦች፣ በአውቶብስ መጠበቂያዎች እና በአጠቃላይ ባንዲራ መቀባት #ፈፅሞ የተከለከለ እንደሆነ ፖሊስ ኮሚሽኑ ለሸገር ተናግሯል፡፡

የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን በከተማዋ ሚስማር የተተከለበትን ዱላ የያዙ ግለሰቦችን እንደተመለከተና #እርምጃ እንደተወሰደ ተናግረዋል፡፡

ከዚህ በኋላም ፖሊስ ኮሚሽኑ አላስፈላጊ የሆኑ ድርጊቶችን ከተመለከተ ፖሊሳዊ እርምጃ እንደሚወስድ አሳውቋል፡፡

የዲፕሎማት መቀመጫ ትልልቅ ጉባኤዎች የሚሰሙባት እና የአፍሪካ መዲና ለሆነችው አዲስ አበባ ደረጃዋን የጠበቀ ሰላምና ፀጥታ እንዲፈጠር ፖሊስ ኮሚሽኑ ከሚመለከታቸው ጋር እየሰራ እንደሆነ ለሸገር ተናግሯል፡፡

©Sheger FM 102.1
@tsegabwolde @tikvahethiopia
የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት መንግስቱ ኃ/ማርያም ፈፅሞ ወደኢትዮጵያ መመለስ አይፈልጉም!

ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም ወደ ኢትዮጰያ ምህረት ቢደረግለትም የመመለስ ፍላጎት የለውም። በዝንቧቤ ለመንግስት ጋዜጣ የሚሰራ አንድ ጋዜጠኛ እንደተናገረው የቀድሞ የኢትዮጰያ ፕሬዝዳንት እና የአሁኑ የዝነንቧቤ ፕሪዝዳንቱ ፀጥታ አማካሪ ኮሎኔል መንግስቱ ኃይለማርያም የኢትዮጰያ መንግስት ከተፈረደበት ፍርድ ምህረት በያደርግለት እንኳን ሀገሩ #ፈፅሞ መሄድ እንደማይፈልግ ጋዜጠኛው ከሶስት ወር በፊት ቢሮው ለስራ በሄደበት እንዳጫወተው ገልጿል። "እድሜው ቢገፋም ሰውነቱ አሁንም ለስራ ብቁ ነው። እኛ ዝምቧቤያዉያን በሚድያ አይተነው #አናውቅም። ቢሮው ስንሄድ የመጫወት ችግር የለበትም። ድምፁን እንድትቀዳ፣ ፎቶ እንድታነሳው ወይንም ማስታወሻ ይዘክ እንድታወራው አይፈልግም። ወዳጁ ሙጋቤ ቢሞትም ፕሬዝዳንት ምንጋጋዋ ለመንግስቱ ከፍተኛ አክብሮት አለው። ወዳጅነታቸውም የቆየ ነው።" ብሏል ጋዜጠኛው።

ምንጭ፦ ተስፋዬ ጌትነት/ከካፒታል ጋዜጣ/
@tsegabwolde @tikvahethiopia