#updateሀዋሳ የኢህአዴግ ጉባኤ⬇️
ኢህአዴግ በ11ኛው ጉባኤው #በርዕዮተ_ዓለም ለውጥ ላይም ሆነ በአርማ ለውጥ ላይ #እንደማይወያይ ተገልጿል። የጉበኤውን ውሎ በተመለከተ መግለጫ የሰጡት የጉባኤው ቃል አቀባይ አቶ ፍቃዱ ተሰማ እንደገለፁት ጉባኤው አጀማመሩ ያማረና ከሌላው ጊዜ በበለጠ በርካቶችን ያሳተፈ ነበር ብለዋል።
የተፎካከሪ ፓርቲዎች መሳተፍ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓና የእስያ ሀገራትን የወከሉ የፓርቲ አመራሮችም በመክፈቻው መገኘታቸው ጉባኤውን #ልዩ እንደሚያደርገው ገልፀዋል።
ጉባኤው ከመክፈቻ ፕሮግራሙ በኋላ በጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ የቀረበለት ሪፖርት ላይ መወያየቱን እና ይህ በነገው ዕለትም እንደሚቀጥል ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል።
ጉባኤው በቆይታው የሚመክርባቸው በርካታ ጉዳዮች ቢኖሩም በርዕዮተ ዓለም ለውጥም ሆነ በስምና አርማ ለውጥ ላይ እንደማይመክር ግን ቃል አቀባዩ አቶ ፍቃዱ ተሰማ አስታውቀዋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia
ኢህአዴግ በ11ኛው ጉባኤው #በርዕዮተ_ዓለም ለውጥ ላይም ሆነ በአርማ ለውጥ ላይ #እንደማይወያይ ተገልጿል። የጉበኤውን ውሎ በተመለከተ መግለጫ የሰጡት የጉባኤው ቃል አቀባይ አቶ ፍቃዱ ተሰማ እንደገለፁት ጉባኤው አጀማመሩ ያማረና ከሌላው ጊዜ በበለጠ በርካቶችን ያሳተፈ ነበር ብለዋል።
የተፎካከሪ ፓርቲዎች መሳተፍ፣ የአፍሪካ፣ የአውሮፓና የእስያ ሀገራትን የወከሉ የፓርቲ አመራሮችም በመክፈቻው መገኘታቸው ጉባኤውን #ልዩ እንደሚያደርገው ገልፀዋል።
ጉባኤው ከመክፈቻ ፕሮግራሙ በኋላ በጉባኤው አዘጋጅ ኮሚቴ የቀረበለት ሪፖርት ላይ መወያየቱን እና ይህ በነገው ዕለትም እንደሚቀጥል ቃል አቀባዩ አስታውቀዋል።
ጉባኤው በቆይታው የሚመክርባቸው በርካታ ጉዳዮች ቢኖሩም በርዕዮተ ዓለም ለውጥም ሆነ በስምና አርማ ለውጥ ላይ እንደማይመክር ግን ቃል አቀባዩ አቶ ፍቃዱ ተሰማ አስታውቀዋል።
ምንጭ፦ የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን
@tsegabwolde @tikvahethiopia