TIKVAH-ETHIOPIA
#ይነበብ🚨 " በወንጀል የተገኘን ንብረት #ህጋዊ_ማስመሰልና #ሽብርተኝነትን_በገንዘብ_የመርዳት ወንጀልን ለመከላከል እና ለመቆጣጠር " የወጣ ረቂቅ አዋጅ ለሕ/ተ/ም/ቤት ቀርቧል። በዚሁ ረቂቅ ላይ በክፍል 5 ' ስለ ምርመራ ' ሰፍሯል። ረቂቁ ስለ #ምርመራ ምን ይላል ? - በወንጀል የተገኘ ንብረት ህጋዊ ማስመሰል ወይም ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ወይም የወንጀል ፍሬን ተከታትሎ ለመለየት…
#ኢትዮጵያ
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን የሚመረምር ሰው፤ በምርመራ ወቅት ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት ከ #ግድያ ውጪ የትኛውንም ዓይነት ወንጀል ቢፈጽም ተጠያቂ የማያደርግ አዋጅ ጸደቀ፡፡
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል፡፡
አዋጁ በሽፋን ስር የሚደረግ ምርመራ (Under cover investigation) እንዲያስፈጽም የተመደበ ሰው፤ በግዴታ ላይ እያለ ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያትና ከፈቃዱ ውጪ በሆነ ከግድያ ወንጀል በስተቀር ለሚፈጽመው የወንጀል ድርጊት የወንጀል ክስ አይቀርብበትም ይላል።
የምክር ቤት አባሉ አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር) በአዋጁ 5/15 ላይ የቀረበው ዐረፍተ ነገር ትንሽ ከባድ መስሎ እንደታያቸው ተናግረው አዋጁ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡
" እንደዚህ ዓይነት አዋጅ በተለይ ሽብርን ለመከላከል ለሀገራችን ያስፈልጋታል " ሲሉ የምክር ቤት አባሉ ተናግረዋል፡፡
‘’ የሆነው ሆኖ ግን ' አንድ ሰው በግዳጅ ላይ እያለ ከግድያ በስተቀር ለሚፈጽመው ወንጀል አይጠየቅም ' ይላል፡፡ አንደኛ ወንጀል ፈጽሟል ይላል፣ ወንጀል ፈጽሞ አለመጠየቅ ትክክለኛ አይመስለኝም፡፡ ወይም ድርጊቶቹ ተዘርዝረው ህጋዊ መብት የተሰጠው ሰው ሚወስዳቸው እርምጃዎች ወንጀል አይደሉም ብለን ማለፍ እንጂ አንድ ሰው በግዳጅ ላይ እያለ ለሚፈጽመው ወንጀል ከግድያ በስተቀር የሚለውን ሰው እንደፈለገ እንዲሆን የሚያደርግ ነው’ " ሲሉ አለሙ (ዶ/ር) ሃሳበቸውን አስረድተዋል፡፡
ሌላ ሙሉቀን አሰፋ የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው " እኔ በግሌ እንደተፎካካሪ የፖለቲካ ሰው አዋጁ ባለሀብቶችን፣ ጋዜጠኞችን፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን እና የታዋቂ ሰዎችን መብት የሚገድብ ነው " ብለዋል፡፡
" እንዲያውም የመናገር መብትን ይከለክላል የሚል እምነት ነው እኔ ያለኝ " ያሉት የምክር ቤት አባሉ ‘" ምክንያቱም አዋጁን ስናየው በ10 ዓመት ገድቦ ነው የወጣው’ " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
" ህግ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ነው ተግባራዊ መደረግ ያለበት’ " ያሉት አቶ ሙሉቀን " ስለዚህ ከ10 ዓመት ወዲህ ብሎ ማውጣቱ የተወሰኑ ግለሰቦችን ወይም ቡድኖችን ለማጥቃት ያሰበ ስለሆነ ለሀገራችንም ጥሩ አይደለም የሚል እምነት አለኝ " ብለዋል፡፡
" በአለም አቀፍ ስምምነቶች ላይ እንደተገለጸው ሀይልን በመጠቀም፣ ንጹሃንን በማስገደድ አላማቸውን ለማስፈጽም የሚሳተፉ ተዋናዮችን ተጠያቂ ለማድረግ ሳይሆን አዋጁ እየዋለ ያለው በዋነኝነት የመንግስት ተቃዋሚዎችን፣ መንግስት ውስጥ ሆነው መንግስትን የሚተቹትን እና ጋዜጠኞችን ነው " ያሉት ደግሞ ሌላው የምክር ቤት አባል የሆኑት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ናቸው፡፡
" የአዋጁን ዝርዝር ካየንው በጣም አስገራሚ የሆኑ ድንጋጌዎችን ይዟል " ያሉት የምክር ቤት አባሉ " ለምሳሌ የፋይናንስ ድህንነት አገልግሎት አጠራጣሪ ግብይትን ለ7 ቀን አግዶ ማቆየት ይችላል ይላል ያውም ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ " ብለዋል፡፡
" አዋጁ በሽፋን ስር ምርመራ የሚያካሄድ መርማሪ ከግድያ ወንጀል ውጭ በሌላ ወንጀል አይጠየቅም ይላል " ያሉት ደሳለኝ ጫኔ(ዶ/ር) " ለምሳሌ መርማሪው በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ተደራድሮ ከሆነ ከወንጀለኛው ጋር መቀበሉን ብናውቅ አይጠየቅም ማለት ነው? ማሰቃየት ቢፈጽም፣ የመብት ጥሰት ቢፈጽም አይጠየቅም ማለት ነው? መሆን ያለበት ግን ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው አለም አቀፍ ድንጋጌዎች የተካተቱ ወንጀሎችን አለመፈጸሙ ነው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ሌላው አቶ ዘካሪያስ የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው " አዋጁ አንዳንድ የምክር ቤት አባላት እንደሚሉት ተቃዋሚን እና የሚዲያ ሰዎችን ለማፈን አይደለም " ብለዋል፡፡
አቶ ሳዲቅ አደም የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው " አዋጁ ጠንከር ያለ መሆኑን ተናግረው ጠንከር ያለበት ምክንያትም ግልጽ ነው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
" ያለንበት ቀጠና አስቸጋሪ ነው፤ ሽብርተኝነት የሚበዛበት በመሆኑ የአዋጁ ከበድ ማለት ተገቢ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ከመብት አንፃር ሊታዩ የሚችሉ ነገሮች አሉ ያሉት አቶ ሳዲቅ ከህገ መንግስታችንም ስንነሳ ፍጹም የሚባል መብት የለም " ብለዋል፡፡
" ከመብቶች ሁሉ የላቀ ዋና መብት የሚባለው በህይወት የመኖር መብት ነው ይህ መብትም ፍጹም አይደለም " ሲሉ የተናገሩት የምክር ቤት አባሉ " ስለዚህ መብት የሚባለው ነገር ለህዝብ፣ ለማህበረሰብ እና ለሀገር ድህንነት ሲባል በየትኛውም ሀገር መብቶችን ፍጹማዊ አድርጎ የሚያስቀምጥ የለም " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
" ስጋት አድርጎ የሚወስድ ወገን ሊኖር ይችላል ግን ለምን ይሰጋል? " ሲሉ የጠየቁት የምክር ቤት አባሉ " ይህ አዋጅ ሲወጣ ለመጠርጠርም መሟላት ያለበት ነገር አለ ማንኛውም ወገን እነዚህ በአዋጁ የተቀመጡ ነገሮችን ካሟላ አይነካም ዋናው መስፈርቱን ማሟላት ነው " ብለዋል፡፡
" አዋጁ የወጣው በንድፍ ሃሳብ የምንፈራቸውን ለመከላከል ሳይሆን በተግባር እያየን እየኖርንበት ያለውን ነው " የሚሉት አቶ ሳደቅ " ሽብርተኝነት በሀገራችን በስፋት አለ ኤ ቤ ሲ ብለን ልንጠራቸው የምንችላቸው ግለሰቦች እና ወገኖች አሉ ስለዚህ ይህን ለመከላከል ለምን እንሰጋለን " ብለዋል፡፡
የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ኢሳ ቦሮ በበኩላቸው በሰጡት ምላሽ የሚደረገው ምርመራ ልዩ መሆኑን ተናግረው አዋጁ አንድን ቡድን ለማጥቃት ታስቦ የወጣ አይደለም ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ምክር ቤቱ በመደበኛ ስብሰባው በማሻሽያ ረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ በሶስት ተቃዉሞ በአንድ ድምጽ ተአቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM
@tikvahethiopia
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳትን የሚመረምር ሰው፤ በምርመራ ወቅት ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያት ከ #ግድያ ውጪ የትኛውንም ዓይነት ወንጀል ቢፈጽም ተጠያቂ የማያደርግ አዋጅ ጸደቀ፡፡
በወንጀል የተገኘ ንብረት ሕጋዊ ማስመሰል እና ሽብርተኝነትን በገንዘብ መርዳት ወንጀልን ለመከላከልና ለመቆጣጠር የወጣው አዋጅ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ጸድቋል፡፡
አዋጁ በሽፋን ስር የሚደረግ ምርመራ (Under cover investigation) እንዲያስፈጽም የተመደበ ሰው፤ በግዴታ ላይ እያለ ከአቅሙ በላይ በሆነ ምክንያትና ከፈቃዱ ውጪ በሆነ ከግድያ ወንጀል በስተቀር ለሚፈጽመው የወንጀል ድርጊት የወንጀል ክስ አይቀርብበትም ይላል።
የምክር ቤት አባሉ አለሙ ጎንፋ (ዶ/ር) በአዋጁ 5/15 ላይ የቀረበው ዐረፍተ ነገር ትንሽ ከባድ መስሎ እንደታያቸው ተናግረው አዋጁ አስፈላጊ ነው ብለዋል፡፡
" እንደዚህ ዓይነት አዋጅ በተለይ ሽብርን ለመከላከል ለሀገራችን ያስፈልጋታል " ሲሉ የምክር ቤት አባሉ ተናግረዋል፡፡
‘’ የሆነው ሆኖ ግን ' አንድ ሰው በግዳጅ ላይ እያለ ከግድያ በስተቀር ለሚፈጽመው ወንጀል አይጠየቅም ' ይላል፡፡ አንደኛ ወንጀል ፈጽሟል ይላል፣ ወንጀል ፈጽሞ አለመጠየቅ ትክክለኛ አይመስለኝም፡፡ ወይም ድርጊቶቹ ተዘርዝረው ህጋዊ መብት የተሰጠው ሰው ሚወስዳቸው እርምጃዎች ወንጀል አይደሉም ብለን ማለፍ እንጂ አንድ ሰው በግዳጅ ላይ እያለ ለሚፈጽመው ወንጀል ከግድያ በስተቀር የሚለውን ሰው እንደፈለገ እንዲሆን የሚያደርግ ነው’ " ሲሉ አለሙ (ዶ/ር) ሃሳበቸውን አስረድተዋል፡፡
ሌላ ሙሉቀን አሰፋ የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው " እኔ በግሌ እንደተፎካካሪ የፖለቲካ ሰው አዋጁ ባለሀብቶችን፣ ጋዜጠኞችን፣ ተፎካካሪ የፖለቲካ ፓርቲዎችን፣ የሰብአዊ መብት ተሟጋቾችን እና የታዋቂ ሰዎችን መብት የሚገድብ ነው " ብለዋል፡፡
" እንዲያውም የመናገር መብትን ይከለክላል የሚል እምነት ነው እኔ ያለኝ " ያሉት የምክር ቤት አባሉ ‘" ምክንያቱም አዋጁን ስናየው በ10 ዓመት ገድቦ ነው የወጣው’ " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
" ህግ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ነው ተግባራዊ መደረግ ያለበት’ " ያሉት አቶ ሙሉቀን " ስለዚህ ከ10 ዓመት ወዲህ ብሎ ማውጣቱ የተወሰኑ ግለሰቦችን ወይም ቡድኖችን ለማጥቃት ያሰበ ስለሆነ ለሀገራችንም ጥሩ አይደለም የሚል እምነት አለኝ " ብለዋል፡፡
" በአለም አቀፍ ስምምነቶች ላይ እንደተገለጸው ሀይልን በመጠቀም፣ ንጹሃንን በማስገደድ አላማቸውን ለማስፈጽም የሚሳተፉ ተዋናዮችን ተጠያቂ ለማድረግ ሳይሆን አዋጁ እየዋለ ያለው በዋነኝነት የመንግስት ተቃዋሚዎችን፣ መንግስት ውስጥ ሆነው መንግስትን የሚተቹትን እና ጋዜጠኞችን ነው " ያሉት ደግሞ ሌላው የምክር ቤት አባል የሆኑት ደሳለኝ ጫኔ (ዶ/ር) ናቸው፡፡
" የአዋጁን ዝርዝር ካየንው በጣም አስገራሚ የሆኑ ድንጋጌዎችን ይዟል " ያሉት የምክር ቤት አባሉ " ለምሳሌ የፋይናንስ ድህንነት አገልግሎት አጠራጣሪ ግብይትን ለ7 ቀን አግዶ ማቆየት ይችላል ይላል ያውም ያለ ፍርድ ቤት ትዕዛዝ " ብለዋል፡፡
" አዋጁ በሽፋን ስር ምርመራ የሚያካሄድ መርማሪ ከግድያ ወንጀል ውጭ በሌላ ወንጀል አይጠየቅም ይላል " ያሉት ደሳለኝ ጫኔ(ዶ/ር) " ለምሳሌ መርማሪው በሚሊዮን የሚቆጠር ገንዘብ ተደራድሮ ከሆነ ከወንጀለኛው ጋር መቀበሉን ብናውቅ አይጠየቅም ማለት ነው? ማሰቃየት ቢፈጽም፣ የመብት ጥሰት ቢፈጽም አይጠየቅም ማለት ነው? መሆን ያለበት ግን ኢትዮጵያ በፈረመቻቸው አለም አቀፍ ድንጋጌዎች የተካተቱ ወንጀሎችን አለመፈጸሙ ነው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
ሌላው አቶ ዘካሪያስ የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው " አዋጁ አንዳንድ የምክር ቤት አባላት እንደሚሉት ተቃዋሚን እና የሚዲያ ሰዎችን ለማፈን አይደለም " ብለዋል፡፡
አቶ ሳዲቅ አደም የተባሉ የምክር ቤት አባል በበኩላቸው " አዋጁ ጠንከር ያለ መሆኑን ተናግረው ጠንከር ያለበት ምክንያትም ግልጽ ነው " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
" ያለንበት ቀጠና አስቸጋሪ ነው፤ ሽብርተኝነት የሚበዛበት በመሆኑ የአዋጁ ከበድ ማለት ተገቢ ነው ሲሉ ተናግረዋል፡፡ ከመብት አንፃር ሊታዩ የሚችሉ ነገሮች አሉ ያሉት አቶ ሳዲቅ ከህገ መንግስታችንም ስንነሳ ፍጹም የሚባል መብት የለም " ብለዋል፡፡
" ከመብቶች ሁሉ የላቀ ዋና መብት የሚባለው በህይወት የመኖር መብት ነው ይህ መብትም ፍጹም አይደለም " ሲሉ የተናገሩት የምክር ቤት አባሉ " ስለዚህ መብት የሚባለው ነገር ለህዝብ፣ ለማህበረሰብ እና ለሀገር ድህንነት ሲባል በየትኛውም ሀገር መብቶችን ፍጹማዊ አድርጎ የሚያስቀምጥ የለም " ሲሉ ተናግረዋል፡፡
" ስጋት አድርጎ የሚወስድ ወገን ሊኖር ይችላል ግን ለምን ይሰጋል? " ሲሉ የጠየቁት የምክር ቤት አባሉ " ይህ አዋጅ ሲወጣ ለመጠርጠርም መሟላት ያለበት ነገር አለ ማንኛውም ወገን እነዚህ በአዋጁ የተቀመጡ ነገሮችን ካሟላ አይነካም ዋናው መስፈርቱን ማሟላት ነው " ብለዋል፡፡
" አዋጁ የወጣው በንድፍ ሃሳብ የምንፈራቸውን ለመከላከል ሳይሆን በተግባር እያየን እየኖርንበት ያለውን ነው " የሚሉት አቶ ሳደቅ " ሽብርተኝነት በሀገራችን በስፋት አለ ኤ ቤ ሲ ብለን ልንጠራቸው የምንችላቸው ግለሰቦች እና ወገኖች አሉ ስለዚህ ይህን ለመከላከል ለምን እንሰጋለን " ብለዋል፡፡
የህግ እና ፍትህ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ምክትል ሰብሳቢ አቶ ኢሳ ቦሮ በበኩላቸው በሰጡት ምላሽ የሚደረገው ምርመራ ልዩ መሆኑን ተናግረው አዋጁ አንድን ቡድን ለማጥቃት ታስቦ የወጣ አይደለም ብለዋል፡፡
በመጨረሻም ምክር ቤቱ በመደበኛ ስብሰባው በማሻሽያ ረቂቅ አዋጁ ላይ ከተወያየ በኋላ በሶስት ተቃዉሞ በአንድ ድምጽ ተአቅቦ እና በአብላጫ ድምጽ አጽድቆታል፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ነው።
#ShegerFM
@tikvahethiopia
❤1.04K😭959😡363🤔66😱28💔28😢20🕊16🙏14🥰5👏5
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ የገቢ ግብር ምጣኔ ላይ ማሻሻያ ለማድረግ መንግስት ረቂቅ አዋጅ ማዘጋጀቱን ሸገር ኤፍ ኤም 102.1 ሬድዮ ጣቢያ ዘግቧል። ሬድዮ ጣቢያው ከገንዘብ ሚኒስቴር አገኘሁት ባለው መረጃ በደመወዝተኛው ሆነ በንግድ የገቢ ግብር ምጣኔ ላይ ማሻሻያዎችን የያዘ ረቂቅ አዋጅ ተዘጋጅቷል። በመጭው ሰኞም በረቂቅ አዋጁ ላይ ከባለሙያዎች ጋር ለመመካከር ጥሪ ማድረጉ ተሰምቷል። የኢትዮጵያ ሰራተኞች ኮንፌዴሬሽንና…
#ኢትዮጵያ
የሠራተኞች መነሻ የደመወዝ ወለል 8,384 ብር እንዲሆን ተጠይቋል።
ወርኃዊ ደመወዛቸው እስከ 8,384 ብር የሆነ ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ለመንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን ገለጸ፡፡
የኢሠማኮ ፕሬዚዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ፥ " ወርኃዊ ደመወዛቸው እስከ 8,384 ብር የሆነ ተቀጣሪ ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲደረጉ ለመንግሥት ጥያቄ አቅርበናል " ብለዋክ።
የገንዘብ ሚኒስቴር ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት በሥራ ላይ ቆይቷል የተባለውን የገቢ ግብር አዋጅ 979/2008ን ለማሻሻል ጉዳዩ ይመለከታቸዋል ከተባሉ ባለድርሻዎች ጋር ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ እስከ ሁለት ሺሕ ብር የሚከፈለቸው ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ ተደንግጓል፡፡
ኢሠማኮ እስከ 8,384 ብር ድረስ የሚከፈለቸው ተቀጣሪዎች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ ለገንዘብ ሚኒስቴር በደብዳቤ እንደጠየቀ አስታውቋል፡፡
አቶ ካሳሁን በዓለም ባንክ መረጃ መሠረት ዕለታዊ ገቢው ከሦስት ዶላር በታች የሆነ ሰው ደሃ በመሆኑ፣ የመንግሥት የገቢ ግብር በዚህ ወለል ሥር ያሉ ተቀጣሪዎችን ታሳቢ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል፡፡
በማናቸውም ቀጣሪ ተቋማት የሚሠሩ ሠራተኞች በወር ከ8,384 ብር እስከ 22,974 ብር ደመወዝ የሚያገኙ ሠራተኞች፣ አሥር በመቶ ግብር እንዲጣልባቸው መንግሥትን መጠየቁን ኢሠማኮ ገልጿል፡፡
ከ22,975 እስከ 44,530 ብር ወርኃዊ ደመወዝ ተከፋዮች የ15 በመቶ፣ ከ44,531 እስከ 72,336 ብር የሚከፈለቸው ደግሞ 20 በመቶ፣ እንዲሁም ከ72,337 እስከ 107,449 ብር የ25 በመቶ ግብር እንዲጣልባቸው ኢሠማኮ በደብዳቤው አሳስቧል።
ከ107,450 እስከ 150,107 ብር ድረስ የሚከፈለቸው ሠራተኞች 30 በመቶ ግብር፣ እንዲሁም 150,108 ብር እና ከዚያ በላይ የሚከፈለቸው ተቀጣሪ ሠራተኞች ደግሞ 35 በመቶ ግብር እንዲከፍሉ ለመንግሥት ባቀረበው ደብዳቤ ኢሠማኮ መጠየቁን ገልጿል።
አሁን በሥራ ላይ ባለው የሠራተኞች የገቢ ግብ አዋጅ መሠረት እስከ 600 ብር ድረስ የሚከፈላቸው ሠራተኞች ከግብር ነፃ ሲሆኑ፣ ከ10,900 ብር ጀምሮ ደግሞ 35 በመቶ ግብር እንዲከፍሉ ይገደዳሉ፡፡
የገንዘብ ሚኒስቴር ከአንድ ሳምንት በፊት ለውይይት ይፋ ባደረገው የገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ 1,200 ብር፣ 1,600 ብር እና 2,000 ብር ወርኃዊ ደመወዝተኞች ከግብር ነፃ እንዲደረጉ ድንጋጌ መኖሩ ይታወሳል።
የመንግሥት የገቢ ግብር ማሻሻያው ሠራተኞች ያለባቸውን ወቅታዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ ታሳቢ ያላደረገ እንደሆነ የተለያዩ የውይይት ተሳታፊዎች አስተያየት መስጠታቸው አይዘነጋም፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
#ሪፖርተርጋዜጣ
@tikvahethiopia
የሠራተኞች መነሻ የደመወዝ ወለል 8,384 ብር እንዲሆን ተጠይቋል።
ወርኃዊ ደመወዛቸው እስከ 8,384 ብር የሆነ ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ የኢትዮጵያ ሠራተኛ ማኅበራት ኮንፌዴሬሽን (ኢሠማኮ) ለመንግሥት ጥያቄ ማቅረቡን ገለጸ፡፡
የኢሠማኮ ፕሬዚዳንት አቶ ካሳሁን ፎሎ ለሪፖርተር ጋዜጣ በሰጡት ቃል ፥ " ወርኃዊ ደመወዛቸው እስከ 8,384 ብር የሆነ ተቀጣሪ ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲደረጉ ለመንግሥት ጥያቄ አቅርበናል " ብለዋክ።
የገንዘብ ሚኒስቴር ላለፉት ዘጠኝ ዓመታት በሥራ ላይ ቆይቷል የተባለውን የገቢ ግብር አዋጅ 979/2008ን ለማሻሻል ጉዳዩ ይመለከታቸዋል ከተባሉ ባለድርሻዎች ጋር ውይይት በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡ በዚህ ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ እስከ ሁለት ሺሕ ብር የሚከፈለቸው ሠራተኞች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ ተደንግጓል፡፡
ኢሠማኮ እስከ 8,384 ብር ድረስ የሚከፈለቸው ተቀጣሪዎች ከግብር ነፃ እንዲሆኑ ለገንዘብ ሚኒስቴር በደብዳቤ እንደጠየቀ አስታውቋል፡፡
አቶ ካሳሁን በዓለም ባንክ መረጃ መሠረት ዕለታዊ ገቢው ከሦስት ዶላር በታች የሆነ ሰው ደሃ በመሆኑ፣ የመንግሥት የገቢ ግብር በዚህ ወለል ሥር ያሉ ተቀጣሪዎችን ታሳቢ ሊያደርግ ይገባል ብለዋል፡፡
በማናቸውም ቀጣሪ ተቋማት የሚሠሩ ሠራተኞች በወር ከ8,384 ብር እስከ 22,974 ብር ደመወዝ የሚያገኙ ሠራተኞች፣ አሥር በመቶ ግብር እንዲጣልባቸው መንግሥትን መጠየቁን ኢሠማኮ ገልጿል፡፡
ከ22,975 እስከ 44,530 ብር ወርኃዊ ደመወዝ ተከፋዮች የ15 በመቶ፣ ከ44,531 እስከ 72,336 ብር የሚከፈለቸው ደግሞ 20 በመቶ፣ እንዲሁም ከ72,337 እስከ 107,449 ብር የ25 በመቶ ግብር እንዲጣልባቸው ኢሠማኮ በደብዳቤው አሳስቧል።
ከ107,450 እስከ 150,107 ብር ድረስ የሚከፈለቸው ሠራተኞች 30 በመቶ ግብር፣ እንዲሁም 150,108 ብር እና ከዚያ በላይ የሚከፈለቸው ተቀጣሪ ሠራተኞች ደግሞ 35 በመቶ ግብር እንዲከፍሉ ለመንግሥት ባቀረበው ደብዳቤ ኢሠማኮ መጠየቁን ገልጿል።
አሁን በሥራ ላይ ባለው የሠራተኞች የገቢ ግብ አዋጅ መሠረት እስከ 600 ብር ድረስ የሚከፈላቸው ሠራተኞች ከግብር ነፃ ሲሆኑ፣ ከ10,900 ብር ጀምሮ ደግሞ 35 በመቶ ግብር እንዲከፍሉ ይገደዳሉ፡፡
የገንዘብ ሚኒስቴር ከአንድ ሳምንት በፊት ለውይይት ይፋ ባደረገው የገቢ ግብር ማሻሻያ ረቂቅ አዋጅ 1,200 ብር፣ 1,600 ብር እና 2,000 ብር ወርኃዊ ደመወዝተኞች ከግብር ነፃ እንዲደረጉ ድንጋጌ መኖሩ ይታወሳል።
የመንግሥት የገቢ ግብር ማሻሻያው ሠራተኞች ያለባቸውን ወቅታዊ የኢኮኖሚ ሁኔታ ታሳቢ ያላደረገ እንደሆነ የተለያዩ የውይይት ተሳታፊዎች አስተያየት መስጠታቸው አይዘነጋም፡፡
ይህ መረጃ ባለቤትነቱ የሪፖርተር ጋዜጣ ነው።
#ሪፖርተርጋዜጣ
@tikvahethiopia
❤3.78K👏674🙏169😭76😡47🕊45🥰36🤔36😱22😢11💔9
#ኢትዮጵያ🇪🇹
ኢትዮጵያ የአለማቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ቁልፍ የህዝብ መረጃ ልውውጥ ስርዓት የአባልነት ማረጋገጫ ተቀበለች።
ኢትዮጵያ 105 አገራትን ባቀፈው የአለማቀፉ አቪዬሽን ድርጅት ቁልፍ የህዝብ መረጃ ልውውጥ ስርዓት (PKD) አባል መሆኗን የሚያረጋግጥ ሰርተፍኬት ከተቋሙ ዋና መቀመጫ ከሆነችው ካናዳ ሞንትሪያል ከሚገኘዉ አለም አቀፉ የሲቪል አቬሽን ተቋም ተቀብላለች።
ኢትዮጵያ የዚህ ማዕቀፍ አባል መሆኗ የኢትዮጵያን ፓስፖርት የያዙ ዜጎች በአባል አገራቱ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ያለምንም እንግልት እንዲጓጓዙ የሚያስችል ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ በየብስም ሆነ በአየር በተጭበረበረ የጉዞ ሰነድ ለመምጣት የሚሞክሩ አካላትን በቀላሉ ለመለየት የሚረዳና በአገር ላይ ሊቃጣ የሚችል የደህንነት ስጋትን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያግዝ ነው።
ኢትዮጵያ ወደዚህ ማዕቀፍ በይፋ መቀላቀሏን ተከትሎ የአለማቀፉ አቪዬሽን ድርጅት አባል አገራት ተወካዮችና የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ሌሎች አካላት በተገኙበት አገሪቱ ያላትን ሁለንተናዊ አቅም የሚያስተዋውቅ መድረክ ተዘጋጅቷል።
በዚህ ወቅትም የኢትዮጵያን የአቪዬሽን ገፅታ፣ የኢሚግሬሽን ስርዓትና አሁናዊ ሁኔታ እንዲሁም የኢትዮጵያን የቱሪዝምና የቢዝነስ አቅሞች የሚያስተዋውቁ ገለፃዎች ተደርገዋል።
በስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት " ኢትዮጵያ የዚህ ማዕቀፍ (PKD) አባል መሆኗ ዜጎች በሚሄዱበት አገር ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ከማድረጉ ባሻገር የአገርን ደህንነት በመጠበቅ ረገድ አይነተኛ ሚና የሚጫወት ይጫወታል " ብለዋል።
" ኢትዮጵያ ጠንካራ በሆነው የአለም አቀፍ አቪዬሽን ትብብር ስርዓት ውስጥ የላቀ ቴክኖሎጂን መጠቀሟ ድንበሯን ከመጠበቅ ባለፈ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ የጋራ ደኅንነት መጠበቅ ያላትን ቁርጠኝነትም የሚያሳይ ውሳኔ ነው " ሱሉ ጠቁመዋል።
የካናዳ ትራንስፖርት ሚኒስትር ምክትል ሚኒስትር ኒኮላስ ሮብሰን " ኢትዮጵያ ወደዚህ ስርዓት በይፋ መቀላቀሏ በአቪዬሽን መስክ የምትሰራውን ስራ በዓለም የታመነ እንዲሆን ያደርጋል " ብለዋል።
" በተለይም በርካታ ዜጎችን ወደ ተለያዩ ክፍለ-ዓለማት የሚያጓጉዝ የግዙፍ አየር መንገድ ባለቤት በመሆኗ ይህን ማዕቀፍ መቀላቀሏ የሚደነቅ ውሳኔ ነው " ሲሉ ጠቁመዋል።
የአለማቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) ፕሬዝዳንት ሳልቫቶሬ ሻኪታኖ ኢትዮጵያ ወደ ማዕቀፉ በመግባት የተሰማቸውን ደስታ በመግለፅ ተቋማቸው የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
መረጃው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
ኢትዮጵያ የአለማቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት ቁልፍ የህዝብ መረጃ ልውውጥ ስርዓት የአባልነት ማረጋገጫ ተቀበለች።
ኢትዮጵያ 105 አገራትን ባቀፈው የአለማቀፉ አቪዬሽን ድርጅት ቁልፍ የህዝብ መረጃ ልውውጥ ስርዓት (PKD) አባል መሆኗን የሚያረጋግጥ ሰርተፍኬት ከተቋሙ ዋና መቀመጫ ከሆነችው ካናዳ ሞንትሪያል ከሚገኘዉ አለም አቀፉ የሲቪል አቬሽን ተቋም ተቀብላለች።
ኢትዮጵያ የዚህ ማዕቀፍ አባል መሆኗ የኢትዮጵያን ፓስፖርት የያዙ ዜጎች በአባል አገራቱ በሚንቀሳቀሱበት ወቅት ያለምንም እንግልት እንዲጓጓዙ የሚያስችል ሲሆን ወደ ኢትዮጵያ በየብስም ሆነ በአየር በተጭበረበረ የጉዞ ሰነድ ለመምጣት የሚሞክሩ አካላትን በቀላሉ ለመለየት የሚረዳና በአገር ላይ ሊቃጣ የሚችል የደህንነት ስጋትን አስቀድሞ ለመከላከል የሚያግዝ ነው።
ኢትዮጵያ ወደዚህ ማዕቀፍ በይፋ መቀላቀሏን ተከትሎ የአለማቀፉ አቪዬሽን ድርጅት አባል አገራት ተወካዮችና የተቋሙ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ሌሎች አካላት በተገኙበት አገሪቱ ያላትን ሁለንተናዊ አቅም የሚያስተዋውቅ መድረክ ተዘጋጅቷል።
በዚህ ወቅትም የኢትዮጵያን የአቪዬሽን ገፅታ፣ የኢሚግሬሽን ስርዓትና አሁናዊ ሁኔታ እንዲሁም የኢትዮጵያን የቱሪዝምና የቢዝነስ አቅሞች የሚያስተዋውቁ ገለፃዎች ተደርገዋል።
በስነስርዓቱ ላይ ንግግር ያደረጉት የኢሚግሬሽንና ዜግነት አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር ወ/ሮ ሰላማዊት ዳዊት " ኢትዮጵያ የዚህ ማዕቀፍ (PKD) አባል መሆኗ ዜጎች በሚሄዱበት አገር ዘመናዊና ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ከማድረጉ ባሻገር የአገርን ደህንነት በመጠበቅ ረገድ አይነተኛ ሚና የሚጫወት ይጫወታል " ብለዋል።
" ኢትዮጵያ ጠንካራ በሆነው የአለም አቀፍ አቪዬሽን ትብብር ስርዓት ውስጥ የላቀ ቴክኖሎጂን መጠቀሟ ድንበሯን ከመጠበቅ ባለፈ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ የጋራ ደኅንነት መጠበቅ ያላትን ቁርጠኝነትም የሚያሳይ ውሳኔ ነው " ሱሉ ጠቁመዋል።
የካናዳ ትራንስፖርት ሚኒስትር ምክትል ሚኒስትር ኒኮላስ ሮብሰን " ኢትዮጵያ ወደዚህ ስርዓት በይፋ መቀላቀሏ በአቪዬሽን መስክ የምትሰራውን ስራ በዓለም የታመነ እንዲሆን ያደርጋል " ብለዋል።
" በተለይም በርካታ ዜጎችን ወደ ተለያዩ ክፍለ-ዓለማት የሚያጓጉዝ የግዙፍ አየር መንገድ ባለቤት በመሆኗ ይህን ማዕቀፍ መቀላቀሏ የሚደነቅ ውሳኔ ነው " ሲሉ ጠቁመዋል።
የአለማቀፉ ሲቪል አቪዬሽን ድርጅት (ICAO) ፕሬዝዳንት ሳልቫቶሬ ሻኪታኖ ኢትዮጵያ ወደ ማዕቀፉ በመግባት የተሰማቸውን ደስታ በመግለፅ ተቋማቸው የሚያደርገውን ድጋፍ አጠናክሮ እንደሚቀጥል አረጋግጠዋል።
መረጃው የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት ነው።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤484😡43👏23🕊13😢8🙏7🤔5
TIKVAH-ETHIOPIA
#HoPR🇪🇹 " በዝቋላ አቦና በተለያዩ ገዳማት ምንም መሳሪያ ያልታጠቁ መናኞች እና የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችን ከሞት እና ከድብደባ ለመታደግ አግባብ ያለው የጸጥታ ሃይል የማይመድበው ለምንድነው ? " - የምክር ቤት አባሉ አበባው ደሳለው (ዶ/ር) የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አባሉና አማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) አባሉ አበባው ደሳለው (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)ን ምን ጠየቁ…
#ኢትዮጵያ🇪🇹
" የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል፤ ከ40 ወራት በኋላም ተጠናቅቆ ስራ ይጀምራል " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
" ኢትዮጵያ ከፍተኛ የማዕድን አቅም ያላት ሀገር ናት፤ በአፍሪካ ውስጥ ትላልቅ የማዕድን አቅም ካላቸው ሀገራት አንዷ ናት ፤ እስካሁን የትክረት የአመራር፣ የዕይታ ማነስ ስለነበረ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ማገዝ ይችል ነበር። አሁን እያነቃቃነው ነው።
ወርቅ ባለፈው ዓመት በዚህ ዓመት 37 ቶን ወርቅ ኤክስፖርት አድርገነዋል። 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ኤክስፖርት ዓመት ያገኘነውም ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተን ስለሰራን ነው። ይህ በየትኛውም ዘመን ያልነበረ ስኬተ ነው። ሌላው ጋዝ ነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በጋዝ ላይ የሚሰማሩ ኩባንያወች ፈቃድ አውጥተው ወደ ተጨባጭ ስራ አይገቡም ነበር።
ኢትዮጵያ የጋዝ ምርት በቅርቡ ለገበያ ማቅረብ ትጀምራለች። በዚህም ሰርቶ አዳሪ እንጂ አውርቶ አዳሪ አለመሆናችንንም በተከታታይ እያሳየን እንቀጥላለን። የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል፤ ከ40 ወራት በኋላም ተጠናቅቆ ስራ ይጀምራል። "
Credit : PMO Ethiopia
@tikvahethiopia
" የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል፤ ከ40 ወራት በኋላም ተጠናቅቆ ስራ ይጀምራል " - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ምን አሉ ?
" ኢትዮጵያ ከፍተኛ የማዕድን አቅም ያላት ሀገር ናት፤ በአፍሪካ ውስጥ ትላልቅ የማዕድን አቅም ካላቸው ሀገራት አንዷ ናት ፤ እስካሁን የትክረት የአመራር፣ የዕይታ ማነስ ስለነበረ የኢትዮጵያን ኢኮኖሚ ማገዝ ይችል ነበር። አሁን እያነቃቃነው ነው።
ወርቅ ባለፈው ዓመት በዚህ ዓመት 37 ቶን ወርቅ ኤክስፖርት አድርገነዋል። 3 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ኤክስፖርት ዓመት ያገኘነውም ከፍተኛ ትኩረት ሰጥተን ስለሰራን ነው። ይህ በየትኛውም ዘመን ያልነበረ ስኬተ ነው። ሌላው ጋዝ ነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ በጋዝ ላይ የሚሰማሩ ኩባንያወች ፈቃድ አውጥተው ወደ ተጨባጭ ስራ አይገቡም ነበር።
ኢትዮጵያ የጋዝ ምርት በቅርቡ ለገበያ ማቅረብ ትጀምራለች። በዚህም ሰርቶ አዳሪ እንጂ አውርቶ አዳሪ አለመሆናችንንም በተከታታይ እያሳየን እንቀጥላለን። የማዳበሪያ ፋብሪካ ግንባታ በቅርቡ ይጀመራል፤ ከ40 ወራት በኋላም ተጠናቅቆ ስራ ይጀምራል። "
Credit : PMO Ethiopia
@tikvahethiopia
😡917❤718😭55👏33🤔31🙏15🕊14😱13💔10🥰8😢5
TIKVAH-ETHIOPIA
#Ethiopia🇪🇹 " አሁን የ2,000 ብር ደሞዝ የለም በሌለ ነገር ከዚያ በታች ያለው ነጻ ነው ብንል ታክስ መቀነስ አይደለም ! " - የምክር ቤት አባል በገቢ ግብር ማሻሽያ አዋጅ ላይ ዝቅተኛ የግብር ከፋይ መነሻ ደመወዝ 5,000 ብር እንዲሆን በምክር ቤት ተጠየቀ፡፡ ይህ ጥያቄ የተጠየቀው የህዝብ ተወካዮች ምክርቤት ዛሬ ከሰዓት በጠራው ልዩ መደበኛ ስብሰባ ላይ ነው፡፡ አሁን በስራ ላይ…
#ኢትዮጵያ🇪🇹
የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ፣ የኑሮ ውድነትን ታሳቢ በማድረግ የገቢ ግብር መነሻ ገቢ ከ2,000 ብር ወደ 5,000 ብር ከፍ እንዲል ጠንካራ ጥያቄ ቀርቧል።
ጥያቄው የቀረበው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ በፓርላማው የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ ባደረገዉ ዉይይት ላይ ነው።
በአሁኑ ረቂቅ አዋጅ መሰረት፣ ከ2,000 ብር በላይ በሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር እንዲከፈል የሚለው ሀሳብ ቀርቧል።
ይህ የገቢ ግብር አዋጅ ከዘጠኝ ዓመታት በላይ ስራ ላይ መዋሉ የተገለጸ ሲሆን፣ አሁን በማሻሻያው ከግብር ነፃ የሚሆነው ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ በ300% በማሳደግ ወደ 2,000 ብር ከፍ እንዲል ተደርጓል።
በተጨማሪም፣ ከፍተኛው የማስከፈያ መጣኔ የሆነው 35% ግብር የሚያርፍበት ገቢ ደግሞ ወደ 14,000 ብር ከፍ እንዲል ሆኗል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ፣ የአዋጁ መሻሻል መንግስት ግብር በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ እንደሚረዳ ገልጸዋል።
ከግብር ከፋዩ ህብረተሰብ የሚነሱ " ግብር በዝቷል ይቀነስ " የሚሉ ሀሳቦች ሚዛናዊ በሆነ መልኩ እንደሚታዩም አክለዋል።
በውይይት መድረኩ ከተነሱት አስተያየቶች መካከል፣፦
- የገቢ ግብር መነሻው ከአምስት ሺህ ብር ጀምሮ እንዲሆን፣
- ለአካል ጉዳተኞች በተለየ መልኩ ግብር እንዲቀነስ፣
- በተለያዩ የሙያና የንግድ ዘርፎች አንፃር በደንብ እንዲታይ የሚሉ ሀሳቦች ቀርበዋል።
የመረጃው ባለቤት የካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ፣ የኑሮ ውድነትን ታሳቢ በማድረግ የገቢ ግብር መነሻ ገቢ ከ2,000 ብር ወደ 5,000 ብር ከፍ እንዲል ጠንካራ ጥያቄ ቀርቧል።
ጥያቄው የቀረበው የፌዴራል የገቢ ግብር አዋጅን ለማሻሻል በቀረበው ረቂቅ አዋጅ ላይ በፓርላማው የፕላን፣ በጀትና ፋይናንስ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ዛሬ ባደረገዉ ዉይይት ላይ ነው።
በአሁኑ ረቂቅ አዋጅ መሰረት፣ ከ2,000 ብር በላይ በሚገኝ ገቢ ላይ 15 በመቶ ግብር እንዲከፈል የሚለው ሀሳብ ቀርቧል።
ይህ የገቢ ግብር አዋጅ ከዘጠኝ ዓመታት በላይ ስራ ላይ መዋሉ የተገለጸ ሲሆን፣ አሁን በማሻሻያው ከግብር ነፃ የሚሆነው ከመቀጠር የሚገኝ ገቢ በ300% በማሳደግ ወደ 2,000 ብር ከፍ እንዲል ተደርጓል።
በተጨማሪም፣ ከፍተኛው የማስከፈያ መጣኔ የሆነው 35% ግብር የሚያርፍበት ገቢ ደግሞ ወደ 14,000 ብር ከፍ እንዲል ሆኗል።
የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ አቶ ደሳለኝ ወዳጄ፣ የአዋጁ መሻሻል መንግስት ግብር በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ጥያቄዎች ለመመለስ እንደሚረዳ ገልጸዋል።
ከግብር ከፋዩ ህብረተሰብ የሚነሱ " ግብር በዝቷል ይቀነስ " የሚሉ ሀሳቦች ሚዛናዊ በሆነ መልኩ እንደሚታዩም አክለዋል።
በውይይት መድረኩ ከተነሱት አስተያየቶች መካከል፣፦
- የገቢ ግብር መነሻው ከአምስት ሺህ ብር ጀምሮ እንዲሆን፣
- ለአካል ጉዳተኞች በተለየ መልኩ ግብር እንዲቀነስ፣
- በተለያዩ የሙያና የንግድ ዘርፎች አንፃር በደንብ እንዲታይ የሚሉ ሀሳቦች ቀርበዋል።
የመረጃው ባለቤት የካፒታል ጋዜጣ ነው።
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤990👏120😭84😡80🕊32🙏24😢11🤔10🥰4😱1
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ዛሬ ወሬ የለም " - ሌ/ጄነራል ታደሰ ወረደ የሃይማኖት አባቶች ልዑክ በመቐለ ! ከአዲስ አበባ ተነስቶ በጥዋቱ ትግራይ ክልል መቐለ አሉላ አባነጋ አውሮፕላን ማረፍያ የደረሰው የሃይማኖት አባቶች ልዑክ ከሁሉም የሃይማኖት ተቋማት የተወጣጣ ሲሆን አጠቃላይ ልዑኩ ከ20 በላይ አባላት አሉት። የሰላም ልኡኩ ከአውሮፕላን ማረፍያ በቀጥታ ወደ መቐለ ፕላኔት ሆቴል አዳራሽ በማመራት በፕሬዜዳንት…
#ኢትዮጵያ🇪🇹
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ፥ " በአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች የሚደረግ ምክክርና እርቀ ሰላም ፍሬው ጣፋጭ ነው " አሉ።
ትናንት ሀምሌ 10/2017 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ያቀኑት የትግራይ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሸማግሌዎች ዛሬ ሀምሌ 11/2017 ዓ.ም ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) መክረዋል።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ከትግራይ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሸማግሌዎች ስለተካሄደው የሰላም ውይይት አስመልከተው በማህበራዊ የትስስር ገፃቸው በትግርኛ ባጋሩት መረጃ " የኢፌዲሪ መንግስት በሽምግልና እና ምክክር ችግሮች እንዲፈቱ ቅድምያ ሰጥቶ እንደሚሰራ በተለያዩ ጊዚያት በተግባር አሳይቷል " ብለዋል።
" በረጅሙ የአገሪቱ የአገረ መንግስት ስርዓት አገራዊ እርቅ ፣ አገራዊ ምክክር ፣ ፓለቲካዊ ውይይት የሚሉ ማህበራዊ አምዶች በኢትዮጵያ ፓለቲካ ውይይት በይፋ እንዲተገበሩ ያደረገው የአሁኑ መንግስት መሆኑ መካድ የለበትም " ብለዋል።
" ግጭት ሌላ ግጭት እየወለደ በችግር አዙሪት ከመኖር ያለፈ ሌላ ፋይዳ የለውም " ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ " በውይይትና መግባባት ችግሮቻችን በመፍታት ሰላምን በፅኑ መሰረት እናኑር " ብለዋል።
" ከተለያዩ የትግራይ የማህበረሰብ ክፍሎች ከተውጣጡ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አካላት ለቀጣይ መደረክ ምቹ መደላድል የሚፈጥር ውይይት አካሂደናል " ሲሉ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተካሄደው ጥልቅ ውይይት በጥያቄና መልስ የታጀቡ በርካታ ጉዳዮች እንደተነሱ ገልጸዋል።
በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አተገባበር ያሉት ተግዳሮቶች እንዴት መታረም አለባቸው ፣ ግጭት ቀስቃሽ የሆኑ ንግግሮች መቆምና መታረም እንዳለባቸው በተለይ የተፈናቃዮችና ትግራይን መልሶ መገንባት ጉዳይ የምክክሩ ዋነኛ ነጥቦች ነበሩ ብለዋል።
የትግራይ ህዝብና ልሂቃን በአገሪቱ ፓለቲካና ኢኮኖሚ በብርቱ ተዋናይ የሚሆኑበት ሁኔታ መፍጠር እጅግ አስፈላጊ እንደሆነና ሌሎች ጉዳዮች ተነስው መግባባት ተደርሶባቸዋል ብለዋል።
" የፌደራል መንግስት ከህዝብ ፣ ከጊዚያዊ አስተዳደሩና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በፓለቲካ በፀጥታና ኢኮኖሚ እንዲሁም በትግራይ መልሶ ግንባታ ዙሪያ ተቀራርበን እንደምንሰራ ደገመን እረጋግጠንላችኋለን " ብለዋል።
የትግራይ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሸማግሌዎች ትናንት ሀምሌ 10/2017 ዓ.ም በመቐለ ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ከተወያዩ በኋላ ወደ አዲስ አበባ በማቅናት ነው ዛሬ ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር ) ጋር ውይይት ያደረጉት ሲል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamliyAA
ፎቶ፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት
@tikvahethiopia
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) ፥ " በአገር ሽማግሌዎችና የሃይማኖት አባቶች የሚደረግ ምክክርና እርቀ ሰላም ፍሬው ጣፋጭ ነው " አሉ።
ትናንት ሀምሌ 10/2017 ዓ.ም ወደ አዲስ አበባ ያቀኑት የትግራይ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሸማግሌዎች ዛሬ ሀምሌ 11/2017 ዓ.ም ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አህመድ (ዶ/ር) መክረዋል።
የኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር) ከትግራይ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሸማግሌዎች ስለተካሄደው የሰላም ውይይት አስመልከተው በማህበራዊ የትስስር ገፃቸው በትግርኛ ባጋሩት መረጃ " የኢፌዲሪ መንግስት በሽምግልና እና ምክክር ችግሮች እንዲፈቱ ቅድምያ ሰጥቶ እንደሚሰራ በተለያዩ ጊዚያት በተግባር አሳይቷል " ብለዋል።
" በረጅሙ የአገሪቱ የአገረ መንግስት ስርዓት አገራዊ እርቅ ፣ አገራዊ ምክክር ፣ ፓለቲካዊ ውይይት የሚሉ ማህበራዊ አምዶች በኢትዮጵያ ፓለቲካ ውይይት በይፋ እንዲተገበሩ ያደረገው የአሁኑ መንግስት መሆኑ መካድ የለበትም " ብለዋል።
" ግጭት ሌላ ግጭት እየወለደ በችግር አዙሪት ከመኖር ያለፈ ሌላ ፋይዳ የለውም " ያሉት ጠቅላይ ሚንስትሩ " በውይይትና መግባባት ችግሮቻችን በመፍታት ሰላምን በፅኑ መሰረት እናኑር " ብለዋል።
" ከተለያዩ የትግራይ የማህበረሰብ ክፍሎች ከተውጣጡ የፐብሊክ ዲፕሎማሲ አካላት ለቀጣይ መደረክ ምቹ መደላድል የሚፈጥር ውይይት አካሂደናል " ሲሉ ገልጸዋል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በተካሄደው ጥልቅ ውይይት በጥያቄና መልስ የታጀቡ በርካታ ጉዳዮች እንደተነሱ ገልጸዋል።
በፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት አተገባበር ያሉት ተግዳሮቶች እንዴት መታረም አለባቸው ፣ ግጭት ቀስቃሽ የሆኑ ንግግሮች መቆምና መታረም እንዳለባቸው በተለይ የተፈናቃዮችና ትግራይን መልሶ መገንባት ጉዳይ የምክክሩ ዋነኛ ነጥቦች ነበሩ ብለዋል።
የትግራይ ህዝብና ልሂቃን በአገሪቱ ፓለቲካና ኢኮኖሚ በብርቱ ተዋናይ የሚሆኑበት ሁኔታ መፍጠር እጅግ አስፈላጊ እንደሆነና ሌሎች ጉዳዮች ተነስው መግባባት ተደርሶባቸዋል ብለዋል።
" የፌደራል መንግስት ከህዝብ ፣ ከጊዚያዊ አስተዳደሩና ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በፓለቲካ በፀጥታና ኢኮኖሚ እንዲሁም በትግራይ መልሶ ግንባታ ዙሪያ ተቀራርበን እንደምንሰራ ደገመን እረጋግጠንላችኋለን " ብለዋል።
የትግራይ የሃይማኖት አባቶችና የአገር ሸማግሌዎች ትናንት ሀምሌ 10/2017 ዓ.ም በመቐለ ከትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር ፕሬዜዳንት ታደሰ ወረደ (ሌ/ጀነራል) ከተወያዩ በኋላ ወደ አዲስ አበባ በማቅናት ነው ዛሬ ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ሚንስትር ዐብይ አሕመድ (ዶ/ር ) ጋር ውይይት ያደረጉት ሲል የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ዘግቧል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamliyAA
ፎቶ፦ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤946😡325🕊101🤔32🙏30😭17🥰10💔9😢4😱3
TIKVAH-ETHIOPIA
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ምንድነው ያሉት ? 🔴 ፕሬዝዳንቱ አብዛኛው ንግግራቸው ስለ ሀገራቸው ኤርትራ የውስጥ ጉዳይ ሳይሆን ስለ ኢትዮጵያ እና ሌሎች ሀገራት ጉዳይ ነበር ! ኤርትራ ትላንት ቅዳሜ 34ኛ ዓመት የነፃነት በዓሏን አክብራለች። ለ34 ዓመታት አገሪቷን በብቸኝነት እያስተዳደሩ ያሉት ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ለ34ኛ ጊዜ ንግግር አድርገዋል። ፕሬዜዳንቱ 20 ደቂቃ ርዝማኔ ባለው ንግግራቸው…
የኤርትራው ፕሬዚዳንት ስለ #ኢትዮጵያ 🇪🇹 ምን እያሉ ነው ?
ከሀገራቸው ጉዳይ ይልቅ ስለ ሰው ሀገር ጉዳዮች ሰፊ ጊዜ ወስደው በመናገርና በመተንተን የሚታወቁት የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ትላንት ምሽት በሀገራቸው ብቸኛው ቴሌቪዥን በተላለፈ ቃለ መጠይቅ #የኢትዮጵያን ስም ደጋግመው ሲያነሱ ታይተዋል።
ፕሬዝዳንቱ ከወራት በፊት በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ከሀገራቸው ጉዳይ ይልቅ ስለ ኢትዮጵያ እና ቀጠናው ጉዳይ ትንታኔ ሲሰጡ እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም። በወቅቱም ኢትዮጵያ ስሟን እያነሱ ለተናገሩት ነገር ሁሉ በቀጥታ አንዳችም ምላሽ ሳትሰጣቸው በዝምታ አልፋቸዋለች።
ትላንት በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ደግሞ ንዴትን በቀላቀለ ሁኔታ በማይመጥኑ ቃላት የኢትዮጵያን ስም ሲያነሱ ነበር።
በተለይም ኢትዮጵያ ያነሳችውን የባህር በር ጥያቄ ሲያጣጥሉት ነው ያመሹት።
የኢትዮጵያን የወደብ እና የባህር በር ጥያቄ " የህጻን ጨዋታ ነው፣ ማሳሳቻ ነው፣ የረከሰ ውሸት ነው ፣ የውስጥ ጉዳይ ማዳፈኛ ነው ፣ ጀርባው የተባበሩት አረብ ኤሜራት የወደብ ማስፋፋት አጀንዳ ነው " የሚሉ ቃላቶችን በመጠቀም ኢትዮጵያን ለማጣጣል ሞክረዋል።
ኢትዮጵያ የባህር በርን ጉዳይ አለም አቀፍ አጀንዳ ማድረጓን ተከትሎ በርካታ ሀገራት ለጥያቄዋ ድጋፍ ማድረጋቸውም ፕሬዝዳንቱን እንዳላስደሰተ የሚጠቁም ንግግርም ሲናገሩ ነበር።
" ፈረንሳይ ከኛ ጋር ናት፣ አሜሪካ ፣ ኤማራት፣ አውሮፓ ህብረት ከኛ ጎን ናቸው ማለት ጭንቅ እንጂ የድል መንገድ አይደለም " በማለት " ኢትዮጵያውያን የውስጥ ችግራችሁን ፍቱ " ሲሉ ተደምጠዋል።
በኢትዮጵያ በኩል ሀገራቸው ላይ የጦርነት ስጋትና ዛቻ እንዳለ በማመላከትም " እራሳችንን እንጠብቃለን " ሲሉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ለባሕር ስትል ኤርትራንም ሆነ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር የመውጋት አንዳችም ፍላጎት እንደሌላት በተደጋጋሚ ማሳወቋ ይታወሳል። ነገር ግን የባህር በር ጉዳይ ህልውናዋ መሆኑን ለዓለም ህዝብ አስረግጣ ተናግራለች።
ሌላው ፕሬዜዳንቱ ኢትዮጵያ ተመድ ሄዳ ከሳናለች (ክሱ ፦ ድንበር አካባቢ አሁንም የኤርትራ ጦር ግፍ እየፈጸመ ስለመሆኑ) " ያሉም ሲሆን " ክሱ አስነዋሪና አሳፋሪ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
ስለ ፕሪቶሪያ ስምምነትም ሲያነሱ ነበር።
ገና የትግራይን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሲፈረም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት እንዳሻከረች በይፋ የሚታወቅ ቢሆንም " ኤርትራን ከመክሰሳችሁ በፊት የፕሪቶሪያን ውል ተግብሩ ፤ የውስጥ ችግራችሁን መፍታት አስቀድሙ ፤ ለምን ስምምነቱ በቅን ልቦና አልተተገበርም ለምን ፋኖ ላይ ጦርነት ከፈታችሁ ? " የሚል ንግግርም ተናግረዋል።
ሌላው የፖለቲካ ፓርቲዎች የሌለባት ፣ የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የማይታወቅባት ኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢትዮጵያን በተመለከተ ንግግራቸው " በኢትዮጵያ መታየት ጀምሮ የነበረው የለውጥ ተስፋ ጨልሟል ፤ የፖለቲካ ፓርቲ ብሎ የለም " የሚል ንግግር አሰምተዋል።
ያለአንዳች ተቀናቃኝ ከ30 ዓመት በላይ ኤርትራን እየገዙ ያሉት ኢሳያስ አፈወርቂ እንደ ሁል ጊዜው የትላንት ምሽቱ ቃለ ምልልሳቸው ስለ ሀገራቸው ጉዳይ ሳይሆን ስለ ኢትዮጵያ እንዲሁም ስለ ሌሎች ሀገራት ጉዳይ በመተንተን ነው ያለፈው።
ከዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ተነሳሽነት በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ሰላም እንዲወርድ ከተደረገ በኃላ የትግራይን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እስኪፈረም ድረስ ኢትዮጵያን እና አስተዳደሯን ሲያሞካሹ እንደቆዩ በአደባባይ የሚታወቅ ሀቅ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamliyMekelle
@tikvahethiopia
ከሀገራቸው ጉዳይ ይልቅ ስለ ሰው ሀገር ጉዳዮች ሰፊ ጊዜ ወስደው በመናገርና በመተንተን የሚታወቁት የኤርትራው ፕሬዜዳንት ኢሳያስ አፈወርቂ ትላንት ምሽት በሀገራቸው ብቸኛው ቴሌቪዥን በተላለፈ ቃለ መጠይቅ #የኢትዮጵያን ስም ደጋግመው ሲያነሱ ታይተዋል።
ፕሬዝዳንቱ ከወራት በፊት በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ከሀገራቸው ጉዳይ ይልቅ ስለ ኢትዮጵያ እና ቀጠናው ጉዳይ ትንታኔ ሲሰጡ እንደነበር የሚዘነጋ አይደለም። በወቅቱም ኢትዮጵያ ስሟን እያነሱ ለተናገሩት ነገር ሁሉ በቀጥታ አንዳችም ምላሽ ሳትሰጣቸው በዝምታ አልፋቸዋለች።
ትላንት በነበራቸው ቃለ መጠይቅ ደግሞ ንዴትን በቀላቀለ ሁኔታ በማይመጥኑ ቃላት የኢትዮጵያን ስም ሲያነሱ ነበር።
በተለይም ኢትዮጵያ ያነሳችውን የባህር በር ጥያቄ ሲያጣጥሉት ነው ያመሹት።
የኢትዮጵያን የወደብ እና የባህር በር ጥያቄ " የህጻን ጨዋታ ነው፣ ማሳሳቻ ነው፣ የረከሰ ውሸት ነው ፣ የውስጥ ጉዳይ ማዳፈኛ ነው ፣ ጀርባው የተባበሩት አረብ ኤሜራት የወደብ ማስፋፋት አጀንዳ ነው " የሚሉ ቃላቶችን በመጠቀም ኢትዮጵያን ለማጣጣል ሞክረዋል።
ኢትዮጵያ የባህር በርን ጉዳይ አለም አቀፍ አጀንዳ ማድረጓን ተከትሎ በርካታ ሀገራት ለጥያቄዋ ድጋፍ ማድረጋቸውም ፕሬዝዳንቱን እንዳላስደሰተ የሚጠቁም ንግግርም ሲናገሩ ነበር።
" ፈረንሳይ ከኛ ጋር ናት፣ አሜሪካ ፣ ኤማራት፣ አውሮፓ ህብረት ከኛ ጎን ናቸው ማለት ጭንቅ እንጂ የድል መንገድ አይደለም " በማለት " ኢትዮጵያውያን የውስጥ ችግራችሁን ፍቱ " ሲሉ ተደምጠዋል።
በኢትዮጵያ በኩል ሀገራቸው ላይ የጦርነት ስጋትና ዛቻ እንዳለ በማመላከትም " እራሳችንን እንጠብቃለን " ሲሉ ተናግረዋል።
ኢትዮጵያ ለባሕር ስትል ኤርትራንም ሆነ የትኛውንም ጎረቤት ሀገር የመውጋት አንዳችም ፍላጎት እንደሌላት በተደጋጋሚ ማሳወቋ ይታወሳል። ነገር ግን የባህር በር ጉዳይ ህልውናዋ መሆኑን ለዓለም ህዝብ አስረግጣ ተናግራለች።
ሌላው ፕሬዜዳንቱ ኢትዮጵያ ተመድ ሄዳ ከሳናለች (ክሱ ፦ ድንበር አካባቢ አሁንም የኤርትራ ጦር ግፍ እየፈጸመ ስለመሆኑ) " ያሉም ሲሆን " ክሱ አስነዋሪና አሳፋሪ ነው " ሲሉ ተደምጠዋል።
ስለ ፕሪቶሪያ ስምምነትም ሲያነሱ ነበር።
ገና የትግራይን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያ የሰላም ስምምነት ሲፈረም ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ግንኙነት እንዳሻከረች በይፋ የሚታወቅ ቢሆንም " ኤርትራን ከመክሰሳችሁ በፊት የፕሪቶሪያን ውል ተግብሩ ፤ የውስጥ ችግራችሁን መፍታት አስቀድሙ ፤ ለምን ስምምነቱ በቅን ልቦና አልተተገበርም ለምን ፋኖ ላይ ጦርነት ከፈታችሁ ? " የሚል ንግግርም ተናግረዋል።
ሌላው የፖለቲካ ፓርቲዎች የሌለባት ፣ የህዝብ እንደራሴዎች ምክር ቤት የማይታወቅባት ኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢትዮጵያን በተመለከተ ንግግራቸው " በኢትዮጵያ መታየት ጀምሮ የነበረው የለውጥ ተስፋ ጨልሟል ፤ የፖለቲካ ፓርቲ ብሎ የለም " የሚል ንግግር አሰምተዋል።
ያለአንዳች ተቀናቃኝ ከ30 ዓመት በላይ ኤርትራን እየገዙ ያሉት ኢሳያስ አፈወርቂ እንደ ሁል ጊዜው የትላንት ምሽቱ ቃለ ምልልሳቸው ስለ ሀገራቸው ጉዳይ ሳይሆን ስለ ኢትዮጵያ እንዲሁም ስለ ሌሎች ሀገራት ጉዳይ በመተንተን ነው ያለፈው።
ከዓመታት በፊት በኢትዮጵያ ተነሳሽነት በኢትዮጵያ እና ኤርትራ መካከል ሰላም እንዲወርድ ከተደረገ በኃላ የትግራይን ጦርነት ያስቆመው የፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት እስኪፈረም ድረስ ኢትዮጵያን እና አስተዳደሯን ሲያሞካሹ እንደቆዩ በአደባባይ የሚታወቅ ሀቅ ነው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamliyMekelle
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤1.41K😡176🕊73🤔48👏40🙏16🥰10😭9😢7💔6😱4
TIKVAH-ETHIOPIA
የኢትዮጵያ_ዓመታዊ_የሰብአዊ_መብቶች_ሁኔታ_ሪፖርት_ከሰኔ_ወር_2016_ዓ_ም_እስከ_ሰኔ_ወር_2017_ዓ.pdf
#ኢትዮጵያ🇪🇹
በሕይወት የመኖር ሁኔታ አሳሳቢ ሆኖ መቀጠሉን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገልጿል።
ይህን የገለጸው ዛሬ በላከልን ዓመታዊ ሪፖርቱ ነው።
" በ2017 በሕይወት የመኖር መብት ሁኔታ አሳሳቢ ሆኖ መቀጠሉን የሚያሳዩ በርካታ ክስተቶች በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተስተውለዋል " ሲል ገልጿል።
በግጭት ዐውድ ውስጥ በቆዩ ወይም በግጭት ውስጥ በሚገኙ አካባቢዎች ፦
- በመንግሥት ኃይሎች፣
- በየአካባቢው በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች፤
- ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች እንዲሁም በእርስ በእርስ ግጭቶች በሰዎች ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት እንደደረሰ አመልክቷል።
በአማራ ክልል በአብዛኛው አካባቢዎች በመንግሥት ኃይሎች እና በታጣቂ ቡድኖች (ፋኖ) መካከል ከ2015 ዓ.ም. መጨረሻ ወራት ጀምሮ በቀጠለው የተራዘመ የትጥቅ ግጭት ዐውድ ውስጥ በተፋላሚ ወገኖች የሚፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች እንደቀጠሉ ገልጿል።
በክልሉ በተራዘመ የትጥቅ ግጭት ውስጥ በቆዩ አካባቢዎች በመንግሥት ኃይሎች እና በታጣቂ ቡድኑ መካከል በተደረጉ የተኩስ ልውውጦች የግጭቱ አካል ያልነበሩ ሰላማዊ ሰዎች ለሞት እና ለአካል ጉዳት እንደተዳረጉ አመልክቷል።
በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በትጥቅ የታገዘ ግጭት ሲካሄድባቸው በቆዩ ቦታዎች የመንግሥት ኃይሎች በሚቆጣጠሩበት ወቅት " ፋኖን ትደግፋላችሁ፣ ትቀልባላችሁ '' ያሏቸው ሰዎች ላይ ግድያ የፈጸሙ ሲሆን፤ መኖሪያ ቤቶችን በእሳት በማቃጠል ጭምር የተፈጸሙ ጥቃቶች ተመዝግበዋል፡፡
የታጠቂ ቡድኑ ("ፋኖ'') አባላት በበቀል ስሜት በወሰዷቸው እርምጃዎች እና " ለሀገር መከላከያ ሰራዊት መንገድ አሳይታችኋል፤ ሰዎችን ጠቁማችሁ አስይዛችኋል " በማለት በሰዎች ላይ ግድያ ፈጽመዋል፡፡ እንዲሁም የመንግሥት ሠራተኞች ወደ ሥራቸው እንዳይመለሱ ማስፈራራታቸውን፣ ወደ ሥራቸው የተመለሱ ሠራተኞች ላይ ግድያ መፈጸማቸውን፤ በተለያዩ አካባቢዎች በመግባት ዘረፋ ማድረጋቸውን፤ በእሳት በማቃጠል ከፍተኛ የንብረት ውድመት ማድረሳቸውን እና ነዋሪዎችን ማፈናቀላቸውን ኢሰመኮ ባከናወናቸው ምርመራዎች እንዳረጋገጠ አሳውቋል።
ኦሮሚያ ክልልን በሚመለከትም በተለያዩ አካባቢዎች በመንግሥት ኃይሎችና በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ኦነግ ሸኔ) መካከል ከሚደረገው የትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ በሰዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እንደቀጠሉ ኢሰመኮ ገልጿል።
በተለያዩ ምክያቶች በሰዎች ላይ የሞት፣ የአካል እና የንብረት ጉዳት ደርሷል፡፡
የመንግሥት ኃይሎች በአንዳንድ አካባቢዎች " ለኦነግ ሽኔ ድጋፍ ታደርጋላችሁ፤ መንገድ ታሳያላችሁ " በሚል በወሰዱት እርምጃ በሰዎች ላይ የሞት ጉዳት ደርሷል፡፡
የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ኦነግ ሸኔ) ታጣቂዎች በተለያየ ምክንያት በተወሰዱ እርምጃዎች በሰዎች ላይ የሞት፣ እገታ፣ የአካል ጉዳት እና የንብረት ውድመት ደርሷል፡፡
ከተለያዩ ከተሞች ወደ አዲስ አበባ ከተማ የሚጓዙ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብሶችን በማስቆም የሚፈጽሟቸው አገታዎች በ2017 የቀጠሉ ሲሆን፤ አጋቾች ከፍተኛ የማስለቀቂያ ገንዘብ ክፍያ በመጠየቅ፤ ገንዘብ ለመክፈል ባልቻሉ ታጋቾች ላይ ግድያን ጨምሮ በርካታ ጥቃቶችን ፈጽመዋል፡፡
ሙሉ ሪፖርት https://tttttt.me/tikvahethiopia/99053
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
በሕይወት የመኖር ሁኔታ አሳሳቢ ሆኖ መቀጠሉን የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ገልጿል።
ይህን የገለጸው ዛሬ በላከልን ዓመታዊ ሪፖርቱ ነው።
" በ2017 በሕይወት የመኖር መብት ሁኔታ አሳሳቢ ሆኖ መቀጠሉን የሚያሳዩ በርካታ ክስተቶች በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች ተስተውለዋል " ሲል ገልጿል።
በግጭት ዐውድ ውስጥ በቆዩ ወይም በግጭት ውስጥ በሚገኙ አካባቢዎች ፦
- በመንግሥት ኃይሎች፣
- በየአካባቢው በሚንቀሳቀሱ የታጠቁ ቡድኖች፤
- ማንነታቸው ባልታወቁ ሰዎች እንዲሁም በእርስ በእርስ ግጭቶች በሰዎች ላይ የሞት እና የአካል ጉዳት እንደደረሰ አመልክቷል።
በአማራ ክልል በአብዛኛው አካባቢዎች በመንግሥት ኃይሎች እና በታጣቂ ቡድኖች (ፋኖ) መካከል ከ2015 ዓ.ም. መጨረሻ ወራት ጀምሮ በቀጠለው የተራዘመ የትጥቅ ግጭት ዐውድ ውስጥ በተፋላሚ ወገኖች የሚፈጸሙ የሰብአዊ መብቶች ጥሰቶች እንደቀጠሉ ገልጿል።
በክልሉ በተራዘመ የትጥቅ ግጭት ውስጥ በቆዩ አካባቢዎች በመንግሥት ኃይሎች እና በታጣቂ ቡድኑ መካከል በተደረጉ የተኩስ ልውውጦች የግጭቱ አካል ያልነበሩ ሰላማዊ ሰዎች ለሞት እና ለአካል ጉዳት እንደተዳረጉ አመልክቷል።
በክልሉ የተለያዩ አካባቢዎች በትጥቅ የታገዘ ግጭት ሲካሄድባቸው በቆዩ ቦታዎች የመንግሥት ኃይሎች በሚቆጣጠሩበት ወቅት " ፋኖን ትደግፋላችሁ፣ ትቀልባላችሁ '' ያሏቸው ሰዎች ላይ ግድያ የፈጸሙ ሲሆን፤ መኖሪያ ቤቶችን በእሳት በማቃጠል ጭምር የተፈጸሙ ጥቃቶች ተመዝግበዋል፡፡
የታጠቂ ቡድኑ ("ፋኖ'') አባላት በበቀል ስሜት በወሰዷቸው እርምጃዎች እና " ለሀገር መከላከያ ሰራዊት መንገድ አሳይታችኋል፤ ሰዎችን ጠቁማችሁ አስይዛችኋል " በማለት በሰዎች ላይ ግድያ ፈጽመዋል፡፡ እንዲሁም የመንግሥት ሠራተኞች ወደ ሥራቸው እንዳይመለሱ ማስፈራራታቸውን፣ ወደ ሥራቸው የተመለሱ ሠራተኞች ላይ ግድያ መፈጸማቸውን፤ በተለያዩ አካባቢዎች በመግባት ዘረፋ ማድረጋቸውን፤ በእሳት በማቃጠል ከፍተኛ የንብረት ውድመት ማድረሳቸውን እና ነዋሪዎችን ማፈናቀላቸውን ኢሰመኮ ባከናወናቸው ምርመራዎች እንዳረጋገጠ አሳውቋል።
ኦሮሚያ ክልልን በሚመለከትም በተለያዩ አካባቢዎች በመንግሥት ኃይሎችና በኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ኦነግ ሸኔ) መካከል ከሚደረገው የትጥቅ ግጭት ጋር በተያያዘ በሰዎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እንደቀጠሉ ኢሰመኮ ገልጿል።
በተለያዩ ምክያቶች በሰዎች ላይ የሞት፣ የአካል እና የንብረት ጉዳት ደርሷል፡፡
የመንግሥት ኃይሎች በአንዳንድ አካባቢዎች " ለኦነግ ሽኔ ድጋፍ ታደርጋላችሁ፤ መንገድ ታሳያላችሁ " በሚል በወሰዱት እርምጃ በሰዎች ላይ የሞት ጉዳት ደርሷል፡፡
የኦሮሞ ነጻነት ሰራዊት (ኦነግ ሸኔ) ታጣቂዎች በተለያየ ምክንያት በተወሰዱ እርምጃዎች በሰዎች ላይ የሞት፣ እገታ፣ የአካል ጉዳት እና የንብረት ውድመት ደርሷል፡፡
ከተለያዩ ከተሞች ወደ አዲስ አበባ ከተማ የሚጓዙ የሕዝብ ማመላለሻ አውቶብሶችን በማስቆም የሚፈጽሟቸው አገታዎች በ2017 የቀጠሉ ሲሆን፤ አጋቾች ከፍተኛ የማስለቀቂያ ገንዘብ ክፍያ በመጠየቅ፤ ገንዘብ ለመክፈል ባልቻሉ ታጋቾች ላይ ግድያን ጨምሮ በርካታ ጥቃቶችን ፈጽመዋል፡፡
ሙሉ ሪፖርት https://tttttt.me/tikvahethiopia/99053
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤450😭218😡26💔19🙏18👏13🕊13😱4😢3🤔2🥰1