🔊 #የጤናባለሙያዎችድምጽ
🔴 “ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ ዘጠኝ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” - የሆስፒታሉ ሠራተኞች
➡️ “ እነርሱ ጋ ብቻ አይደለም ያልተከፈለው፤ ከ2000 በላይ ሠራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ ” - የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ፣ የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ባለሙያዎች “ በጸጥታ አካላት ድብደባና እስራት ተፈጽሞባቸዋል ” ሲሉ ሠራተኞቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
ተፈጽሟል ስላሉት እስራትና ድብደባ ምክንያት ምን እንደሆነ ሲገልጹ፣ እንደ ሀገር የተደረገው የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ መደረጉን ተከትሎ መሆኑን ሠራተኞቹ አስረድተዋል።
የአራት ወራት የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ከ150 በላይ ለሚሆኑ የሆስፒታሉ ሠራተኞች አለመፈጸሙን፣ እስከ የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ/ም እንዲፈጸምላቸውና እስከተጠቀሰው ጊዜ ድረስ ካልተፈጸመላቸው ሥራ የማቆም አድማ ለማድረግ እንደሚገደዱ በደብዳቤ ጭምር ማሳወቃቸውን ገልጸዋል።
በመሆኑም ክፍያው ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ እንዳደረጉ፣ የተወሰኑት ሥራ ማቆም አድማ ያላደረጉ ሰራተኞች ቢሮ ባሉበት “ አድማ አስመትታችኋል ” በሚል እስራትና ድብደባ እንደተፈጸመባቸው በመግለጽ አማረዋል።
በዚህም፣ “የካቲት 10 እና 11 ቀን 2017 ዓ/ም ሥራ አልገባንም። በቀን 12/2017 ዓ/ም ደግሞ ሙሉ ፓትሮል ፓሊስ መጥቶ በሥራ ላይ የነበሩ የማኔጅመንት አባላትን ይዘው ወጡ ” በማለት ተናግረዋል።
አክለው፣ “ ከየቤቱ ያሉት ሠራተኞችም መረጃው ደርሷቸው ‘ካሰራችሁ ሁላችንንም እሰሩን የሁላችንም ጉዳይ ነው’ ብለው እስሩ ከተፈጸመበት ፓሊስ ጣቢያ ድረስ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል ” ሲሉ ሁነቱን አስረድተዋል።
የታሰሩት ምን ያክል ግለሰቦች ናቸው? ስንል የጠየቅናቸው ሠራተኞቹ በሰጡት ምላሽ፣ “የታሰሩት የሆስፓታሉ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላት ናቸው፡፡ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ 9 ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሠራተኞቹን ቅሬታ በመያዝ፣ ድርጊቱ ለምን እንደተፈጸመ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮን ምላሽ የጠየቀ ሲሆን፣ እስራቱ መፈጸሙን እና ደመወዙ አለመከፈሉን አምኖ ምላሽ ያለውን ሰጥቷል።
የመምሪያው ኃላፊ አቶ አንዱዓለም ማሞ በዝርዝር ምን መለሱ ?
“ ባለሙያዎቹ የካቲት 7 መጥተው ነበር። ከኛ ጋ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይት ካደረግን በኋላ ፕሮሰስ እያደረግን ለማክሰኞ ጠዋት ክልል ቀጠሮ እንደነበረ ገልጸንላቸው ነበር፡፡ ማክሰኞ ሂደን ዘጠኝ ሰዓት ላይ ምላሽ ታገኛላችሁ ብለናቸው ነበር፡፡
እነሱ ጋ ብቻ አይደለም ክፍያው ያልተከፈለው ከ2000 በላይ ሰራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ፡፡ እንደ ዞንም ሶስት ሆስፒታል ላይ ነው ክፍያው ያልተከፈለው፡፡ የተለያዩ የጤና ባለሙያዎችም በወረዳ ደረጃ ያልተከፈላቸው አሉ፡፡
በሦስቱ ሆስፒታሎች ነው ያልተፈጸመው። ግን ሁለቱ ሆስፒታሎች የስራ ማቆም አድማ አላደረጉም፡፡ እነርሱ ግን ለማክሰኞ ቀጥረናቸው እያለ ቀጠሮውን አንቀበልም ብለው ሙያዊ ሥነ ምግባር በማይፈቅድ መንገድ ስራ የማመጽ ነገር አድርገው ነበር።
ግን የተወሰኑ ልጆች ደግሞ ስራ ገበታ ላይ ተገኝተው ነበር፡፡ ስለዚህ ኦሬዲ ድስከስ አድርገን ጉዳዩን ፈተን ልጆቹ ስራ ጀምረዋል አሁን፡፡ ስራ ላይ ናቸው ሁሉም ” ብለዋል።
ታሰሩ የተባሉት የሆስፒታሉ ባልደረቦች ሳይፈቱ እንዴት ሁሉም ስራ ላይ ሊገኙ እንደቻሉ ምላሽ የጠይቅናቸው ኃላፊው፣ “እነርሱ ያልተገባ አካሄድ የሄዱ አሉ፡፡ ከስነ ስርዓት ውጭ ያልተፈቀደ ሰልፍ የወጡበት ሂደትም አለ፡፡ እንግዲህ ከእስር እንዲወጡ እየተሰራ ያለበት ሂደት አለ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ሠራተኞቹ ቅሬታ ያቀረቡት የአራት ወራት ገደማ ደመወዝ አለመጨመሩን ተከትሎ ነውና የመብት ጥያቄ በመቅረቡ እስርና ድብደባ መፈጸም አግባብ ነው? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ጥያቄ አቅርቧል።
አቶ አንዷለም በሰጡት ማብራሪያ፣ “ሠራተኞቹና ባለሙያዎቹ፣ ‘የፈጸምናቸው ድርጊቶች ትክክል አይደሉም ህዝቡን በድለናል ብለው’ ይቅርታ ጠይቀው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡ ከአጠቃላይ ሰራተኞች ውይይት ተደርጎ ጤናማ ስራ ጀምረዋል አሁን” ሲሉ አስተባብለዋል።
ይቅርታ የጠየቁት ማን ናቸው? ሰራተኞቹ ወይስ አሳሪዎቹ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም ኃላፊው፣ “ሰራተኞቹ ” ሲል የመለሰ ሲሆን፣ ታስረው እያለ እንዴት ይቅርታ ይጠይቃሉ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ በድጋሚ ጥያቄ አቅርቧል።
እሳቸውም፣ “ሙያዊ ክብር በጣሰ መልኩ ሰልፍ የወጡትም ይቅርታ እየጠየቁ ነው ያሉት አሁን፡፡ ‘እነርሱ ናቸው ጥፋተኛ’ በሚል ልከውልናል ቤተሰቦቻቸው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
የተወሰኑት ሠራተኞች የስራ ማቆም አድማ አድርገው ነበር፤ በአንጻሩ ደግሞ የተወሰኑት ደግሞ ስራ ላይ ተገኝተው ነበር፤ ነገርግን ‘ሌሎቹን አሳምጻችኋል’ በሚል ስራ የገቡትም ናቸው የታሰሩት። ሥራ ላይ እያሉ ታስረው ሳለ “ይቅርታ ጠይቀዋል” መባሉ ምን ማለት እንደሆም በድጋሚ ምላሽ ጠይቀናል።
አቶ አንዷለም በምላሻቸው፣ “ነገሩ እንግዲህ እንደዚሁ ነው። አሁን ውይይት ላይ ነን፡፡ እነርሱ የሰሩት ጥፋት ስለነበረ ነው የተጠየቁት። አሁን ይቅርታ ጠይቀው ውይይት ላይ ነን ችግሩን ለመፍታት” ነው ያሉት፡፡
እንዳጠቃላይ ችግሩን ለመፍታትስ ምን እየተሰራ ነው? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ “አሁን በጀቱ እውቅና አግኝቷል፡፡ ለሰራተኞች የጸደቀላቸው በጀት እጃችን ላይ ገብቷል፡፡ የክፍያ ሂደት ለማመቻቸት ጥረት እየተደረገ ነው” ብለዋል።
“ከክልል ፋይናንስ ገንዘብ እንድለቀቅ ሂደት ላይ እንደሆነና ያው ከዚያ እንደተለቀቀ ክፍያ እንደሚከፈል ተግባቦት ላይ ተደርሷል” ሲሉም አክለዋል፡፡
(ጉዳዩን እስከመጨረሻ የምንከታተለው ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ ዘጠኝ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” - የሆስፒታሉ ሠራተኞች
➡️ “ እነርሱ ጋ ብቻ አይደለም ያልተከፈለው፤ ከ2000 በላይ ሠራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ ” - የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ
በጌዴኦ ዞን ይርጋጨፌ ከተማ፣ የይርጋጨፌ ሆስፒታል ጤና ባለሙያዎችና የአስተዳደር ባለሙያዎች “ በጸጥታ አካላት ድብደባና እስራት ተፈጽሞባቸዋል ” ሲሉ ሠራተኞቱ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናገሩ።
ተፈጽሟል ስላሉት እስራትና ድብደባ ምክንያት ምን እንደሆነ ሲገልጹ፣ እንደ ሀገር የተደረገው የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ መደረጉን ተከትሎ መሆኑን ሠራተኞቹ አስረድተዋል።
የአራት ወራት የደመወዝ ጭማሪ ክፍያ ከ150 በላይ ለሚሆኑ የሆስፒታሉ ሠራተኞች አለመፈጸሙን፣ እስከ የካቲት 10 ቀን 2017 ዓ/ም እንዲፈጸምላቸውና እስከተጠቀሰው ጊዜ ድረስ ካልተፈጸመላቸው ሥራ የማቆም አድማ ለማድረግ እንደሚገደዱ በደብዳቤ ጭምር ማሳወቃቸውን ገልጸዋል።
በመሆኑም ክፍያው ባለመፈጸሙ የሥራ ማቆም አድማ እንዳደረጉ፣ የተወሰኑት ሥራ ማቆም አድማ ያላደረጉ ሰራተኞች ቢሮ ባሉበት “ አድማ አስመትታችኋል ” በሚል እስራትና ድብደባ እንደተፈጸመባቸው በመግለጽ አማረዋል።
በዚህም፣ “የካቲት 10 እና 11 ቀን 2017 ዓ/ም ሥራ አልገባንም። በቀን 12/2017 ዓ/ም ደግሞ ሙሉ ፓትሮል ፓሊስ መጥቶ በሥራ ላይ የነበሩ የማኔጅመንት አባላትን ይዘው ወጡ ” በማለት ተናግረዋል።
አክለው፣ “ ከየቤቱ ያሉት ሠራተኞችም መረጃው ደርሷቸው ‘ካሰራችሁ ሁላችንንም እሰሩን የሁላችንም ጉዳይ ነው’ ብለው እስሩ ከተፈጸመበት ፓሊስ ጣቢያ ድረስ ሰላማዊ ሰልፍ ወጥተዋል ” ሲሉ ሁነቱን አስረድተዋል።
የታሰሩት ምን ያክል ግለሰቦች ናቸው? ስንል የጠየቅናቸው ሠራተኞቹ በሰጡት ምላሽ፣ “የታሰሩት የሆስፓታሉ ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላት ናቸው፡፡ የጸጥታ አካላት ሆስፒታል ድረስ በመምጣት ድብደባ ፈጽመዋል፣ 9 ሠራተኞችና የማኔጅመንት አባላትን አስረዋል ” ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሠራተኞቹን ቅሬታ በመያዝ፣ ድርጊቱ ለምን እንደተፈጸመ የጌዴኦ ዞን ጤና መምሪያ ቢሮን ምላሽ የጠየቀ ሲሆን፣ እስራቱ መፈጸሙን እና ደመወዙ አለመከፈሉን አምኖ ምላሽ ያለውን ሰጥቷል።
የመምሪያው ኃላፊ አቶ አንዱዓለም ማሞ በዝርዝር ምን መለሱ ?
“ ባለሙያዎቹ የካቲት 7 መጥተው ነበር። ከኛ ጋ ውይይት አድርገዋል፡፡ ውይይት ካደረግን በኋላ ፕሮሰስ እያደረግን ለማክሰኞ ጠዋት ክልል ቀጠሮ እንደነበረ ገልጸንላቸው ነበር፡፡ ማክሰኞ ሂደን ዘጠኝ ሰዓት ላይ ምላሽ ታገኛላችሁ ብለናቸው ነበር፡፡
እነሱ ጋ ብቻ አይደለም ክፍያው ያልተከፈለው ከ2000 በላይ ሰራተኞች እንደ ዞን ያልተከፈላቸው አሉ፡፡ እንደ ዞንም ሶስት ሆስፒታል ላይ ነው ክፍያው ያልተከፈለው፡፡ የተለያዩ የጤና ባለሙያዎችም በወረዳ ደረጃ ያልተከፈላቸው አሉ፡፡
በሦስቱ ሆስፒታሎች ነው ያልተፈጸመው። ግን ሁለቱ ሆስፒታሎች የስራ ማቆም አድማ አላደረጉም፡፡ እነርሱ ግን ለማክሰኞ ቀጥረናቸው እያለ ቀጠሮውን አንቀበልም ብለው ሙያዊ ሥነ ምግባር በማይፈቅድ መንገድ ስራ የማመጽ ነገር አድርገው ነበር።
ግን የተወሰኑ ልጆች ደግሞ ስራ ገበታ ላይ ተገኝተው ነበር፡፡ ስለዚህ ኦሬዲ ድስከስ አድርገን ጉዳዩን ፈተን ልጆቹ ስራ ጀምረዋል አሁን፡፡ ስራ ላይ ናቸው ሁሉም ” ብለዋል።
ታሰሩ የተባሉት የሆስፒታሉ ባልደረቦች ሳይፈቱ እንዴት ሁሉም ስራ ላይ ሊገኙ እንደቻሉ ምላሽ የጠይቅናቸው ኃላፊው፣ “እነርሱ ያልተገባ አካሄድ የሄዱ አሉ፡፡ ከስነ ስርዓት ውጭ ያልተፈቀደ ሰልፍ የወጡበት ሂደትም አለ፡፡ እንግዲህ ከእስር እንዲወጡ እየተሰራ ያለበት ሂደት አለ” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።
ሠራተኞቹ ቅሬታ ያቀረቡት የአራት ወራት ገደማ ደመወዝ አለመጨመሩን ተከትሎ ነውና የመብት ጥያቄ በመቅረቡ እስርና ድብደባ መፈጸም አግባብ ነው? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ ተጨማሪ ጥያቄ አቅርቧል።
አቶ አንዷለም በሰጡት ማብራሪያ፣ “ሠራተኞቹና ባለሙያዎቹ፣ ‘የፈጸምናቸው ድርጊቶች ትክክል አይደሉም ህዝቡን በድለናል ብለው’ ይቅርታ ጠይቀው ወደ ስራ ገብተዋል፡፡ ከአጠቃላይ ሰራተኞች ውይይት ተደርጎ ጤናማ ስራ ጀምረዋል አሁን” ሲሉ አስተባብለዋል።
ይቅርታ የጠየቁት ማን ናቸው? ሰራተኞቹ ወይስ አሳሪዎቹ? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም ኃላፊው፣ “ሰራተኞቹ ” ሲል የመለሰ ሲሆን፣ ታስረው እያለ እንዴት ይቅርታ ይጠይቃሉ? ሲል ቲክቫህ ኢትዮጵያ በድጋሚ ጥያቄ አቅርቧል።
እሳቸውም፣ “ሙያዊ ክብር በጣሰ መልኩ ሰልፍ የወጡትም ይቅርታ እየጠየቁ ነው ያሉት አሁን፡፡ ‘እነርሱ ናቸው ጥፋተኛ’ በሚል ልከውልናል ቤተሰቦቻቸው” የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
የተወሰኑት ሠራተኞች የስራ ማቆም አድማ አድርገው ነበር፤ በአንጻሩ ደግሞ የተወሰኑት ደግሞ ስራ ላይ ተገኝተው ነበር፤ ነገርግን ‘ሌሎቹን አሳምጻችኋል’ በሚል ስራ የገቡትም ናቸው የታሰሩት። ሥራ ላይ እያሉ ታስረው ሳለ “ይቅርታ ጠይቀዋል” መባሉ ምን ማለት እንደሆም በድጋሚ ምላሽ ጠይቀናል።
አቶ አንዷለም በምላሻቸው፣ “ነገሩ እንግዲህ እንደዚሁ ነው። አሁን ውይይት ላይ ነን፡፡ እነርሱ የሰሩት ጥፋት ስለነበረ ነው የተጠየቁት። አሁን ይቅርታ ጠይቀው ውይይት ላይ ነን ችግሩን ለመፍታት” ነው ያሉት፡፡
እንዳጠቃላይ ችግሩን ለመፍታትስ ምን እየተሰራ ነው? ስንል ላቀረብነው ጥያቄም፣ “አሁን በጀቱ እውቅና አግኝቷል፡፡ ለሰራተኞች የጸደቀላቸው በጀት እጃችን ላይ ገብቷል፡፡ የክፍያ ሂደት ለማመቻቸት ጥረት እየተደረገ ነው” ብለዋል።
“ከክልል ፋይናንስ ገንዘብ እንድለቀቅ ሂደት ላይ እንደሆነና ያው ከዚያ እንደተለቀቀ ክፍያ እንደሚከፈል ተግባቦት ላይ ተደርሷል” ሲሉም አክለዋል፡፡
(ጉዳዩን እስከመጨረሻ የምንከታተለው ይሆናል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
😭561😡199❤129🙏24👏23🤔22😱13😢13🕊12🥰3
🔴 " በየጊዜው ቃል ከመግባት የዘለለ ምንም መፍትሄ የሰጠን አካል የለም !! " - የጤና ባለሙያዎች
➡️ " ከ8 ወራት በላይ የትርፍ ሰዓት ክፍያ ስላልተከፈለን ለ2ኛ ጊዜ ስራ ለማቆም እየተገደድን ነዉ !! "
በማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ሎካ-አባያ ወረዳ ሀንጣጤ ሆስፒታል የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች በበዓላት፣ በማታና የእረፍት ቀናት የሰሩበት ከ6 እስከ 9 ወራት የትርፍ ሰዓት ክፍያ ስላልተከፈላቸዉ ለሁለተኛ ጊዜ ስራ ለማቆም እየተገደዱ መሆኑን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
በቁጥር 102 የሚሆኑ የጤና ባለሙያዎቹ ተፈራርመዉ ለሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳድር በአድራሻ በፃፉትና ለሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ፣ ለሎካ አባያ ወረዳ እና ለማዕከላዊ ሲዳማ ዞን አስተዳዳሪ እንዲሁም ለሲዳማ ክልል ጤና ቢሮና ለክልሉ ብልፅግና ፓርቲ በግልባጭ ባስታወቁት የቅሬታ ማመልከቻ ከ2013 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 2017 ዓ/ም የያዝነዉ ወር ድረስ በተለያዩ ጊዜያት ያልተከፈለ በእያንዳንዱ ሠራተኛ ከ6 እስከ 9 ወር ድረስ የትርፍ ሰዓት ክፍያ እንዳልተከፈላቸዉና በዚህም ለልዩ ልዩ ችግሮች መዳረጋቸውን ገልፀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ያነጋገራቸዉ የጤና ባለሙያዎች ቅሬታቸዉን በየደረጃው ለሚመለከታቸው አካላት ሲያቀርቡ ቢቆዩም በየጊዜው ቃል ከመግባት የዘለለ ምንም መፍትሄ የሰጠን አካል የለም ብለዋል።
" ባሳለፍነዉ ዓመት በተመሳሳይ መልኩ የትርፍ ሰዓት ክፍያ በወቅቱ ባለመከፈሉ ምክንያት ለአንድ ወር ሙሉ የስራ ተዘግቶ ነበር " የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ " አሁንም ያለዉ ሁኔታ ወደዚያ እያመራ ነዉ" ብለዋል።
በተለያዩ ጊዜያት ያልተከፈላቸውን የትርፍ ሰዓት ክፍያ በሰራተኞች ቁጥርና ባልተከፈላቸዉ ወር ተባዝቶ ከ2.4 ሚሊዮን ብር በላይ እንደሆነ የሚገልፁት ሰራተኞቹ ፤ የኑሮዉ ጫና ተጨምሮበት ቀርቶ በቀደሙት ጊዜያት እንኳን ያለ ክፍያ እየተመላለሱ መስራት አዳጋች በመሆኑ ለዘርፈ ብዙ ችግሮች መጋለጣቸዉን ተናግረዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሠራተኞችን ቅሬታ ሰምቶ የሎካ አባያ ወረዳ አስተዳዳሪና የማዕከላዊ ሲዳማ ዞን አስተዳዳሪን በጉዳዩ ዙሪያ አነጋግሯቸዋል።
የሎካ አባያ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዘሪሁን ጥላሁን የሀንጣጤ ሆስፒታል ለሎካ አባያ ወረዳ ብቻ ሳይሆን ለአጎራባች አከባቢዎችም ጭምር አገልግሎት የሚሰጥ ሲሆን ከዚህ ቀደም የነበሩ አመራሮች በሆስፒታሉ አሰራር ዉስጥ ጣልቃ በመግባት የሰራተኞች የትርፍ ሰዓት ክፍያ ብቻ ሳይሆን የጥቅማጥቅምና ሌሎችንም በጀቶች በማጉደል በአሁኑ ወቅት በሕግ ቁጥጥር ስር መሆናቸውን ተናግረዉ ለሆስፒታሉ ሰራተኞች ያልተከፈላቸዉ የትርፍ ሰዓት ክፍያ ከወረዳዉ አቅምና በላይ ነዉ ብለዋል።
የማዕከላዊ ሲዳማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ መንግስቱ ማቴዎስ በበኩላቸው የሕክምና ባለሙያዎች እንዲሁም ሕብረተሰቡ የሚያነሷቸዉ ቅሬታዎች ተገቢ መሆናቸውን በመግለፅ የችግሩ መንስኤ የቀድሞ የወረዳዉ አመራርና የሆስታሉ ስራ አስኪያጅ ባደረጉት የሃብት ብክነትና ሌብነት መሆኑን ጠቁመዉ እሳቸው ወደ ዞን አስተዳዳሪነት ከመጡ ወዲህ የሆስፒታሉም የቦርድ ሰብሳቢ መሆናቸዉንና ነባሩን አመራር ከስልጣን እንዲወርድና በሕግ እንዲጠየቅ በማድረግ ከነበረዉ 13 ወራት የትርፍ ሰዓት ክፍያ ዉዝፍ የተወሰኑ ወራት እንዲከፈል መደረጉን ተናግረዋል።
ችግሩ በሀንጣጤ ሆስፒታል ብቻ ሳይሆን በሌሎችም የጤና ጣቢያዎች ጭምር ያለ በመሆኑ በወረዳዉና በዞኑ በጀት ለመሸፈን ከአቅም በላይ ስለሆነ ከክልሉ ብድር መጠየቃቸዉንና በቀጣይ ሳምንት ጊዜ ዉስጥ የቀሪ ወራቶችን ክፍያ በሙሉ ለሙሉ ለመክፈል መዘጋጀታቸዉን ገልፀዋል።
#TikvahEthiopiaFamilyHW
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
😭131❤53😢16🕊11😡8😁3🤔2
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " ተመላላሽ የሕክምና ቀጠሮ ቢኖረንም ሆስፒታሉ ዝግ ስለሆነ አገልግልት ማግኘት አልቻልንም " - ተገልጋዮች ➡️ " ከ6 እስከ 9 ወራት ታግሰን የትርፍ ሰዓት ክፍያ ባለመከፈሉ ከአቅማችን በላይ ሆኖ ስራ አቁመናል" - የጤና ባለሙያዎች 🔴 " የትርፍ ሰዓት ክፍያ አልተከፈለንም ብለዉ መደበኛ ስራቸዉን በሚያቆሙ ላይ ሕጋዊ እርምጃ እንወስዳለን " - የዞን አስተዳዳሪ በሲዳማ ክልል ማዕከላዊ…
#Update
#የጤናባለሙያዎችድምጽ
" የሆስፒታሉን ሜዲካል ዳይሬክተር ጨምሮ 14 የሚሆኑ የጤና ባለሙያዎች እና አስተዳደር ሰራተኞች ከስራ ቦታቸዉ ተወስደው ታስረዋል " - የሀንጣጤ ሆስፒታል ባለሙያዎች
" ' ለሚዲያ መረጃ ስለሰጣችሁ ሚዲያ የሚከፍላችሁ መስሏችኋል ' የሚሉ አመራሮችም አሉ ! "
በሲዳማ ክልል፤ ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ሎካ አባያ ወረዳ በሚገኘዉ ሀንጣጤ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ከ8 ወራት በላይ የትርፍ ሰዓት ክፊያ ባለመከፈሉ ለሎካ አባያ ወረዳ፣ ለማዕከላዊ ሲዳማ ዞንና ለሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ በደብዳቤ ካሳወቁ በኋላ የትርፍ ሰዓት ስራ ማቆማቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ማሳወቃቸው ይታወሳል።
በወቅቱ ስለ ጉዳዩ ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የማዕከላዊ ሲዳማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ መንግስቱ ማቴዎስ ፥ የሠራተኛዉ ጥያቄ ትክክለኛ መሆኑን ገልፀዉ ክፍያዉ እንዲፈፀም ከክልሉ መንግስት ብድር መጠየቃቸዉንና በቅርቡ እንደሚከፈላቸዉ ገልፀዉ የነበረ ሲሆን " የትርፍ ሰዓት ስራ ማቆም መብታቸዉ ነዉ " ሲሉ ገልጸውም ነበር።
ትላንት የሆስፒታሉ ሠራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት " ሁሉም ሰራተኛ በአንድነት ተፈራርሞ ባስገባዉ ደብዳቤ መሰረት ከባለፈዉ ሳምንት ጀምሮ የትርፍ ሰዓት ስራ ብቻ ያቆሙ ቢሆንም የሆስፒታሉን ሜዲካል ዳይሬክር እና 7 የማኔጀመንት አካላትን ጨምሮ 14 የሚሆኑ የሆስፒታሉ ባለሙያዎችን ፖሊስ ከስራ ቦታቸዉ ጭምር ወስዶ አስሯቸዋል " ብለዋል።
" ሁሉም ሠራተኛ የትርፍ ሰዓት ስራ ማቆሙ ሰበብ ተደርጎ በመደበኛ ስራዉ ላይ እንከን እንዳይፈለግበትና ላለመከሰስ የስራ ሰዓቱን በአግባቡ እየተጠቀመ ነዉ " የሚሉት ሠራተኞቹ " ትላንት ጠዋት በድንገት 2 ዶክተሮች፣ 7 ነርሶችንና ሌሎች ባለሙያዎችን 'ትፈለጋላችሁ' በሚል ያለ ፍርድ ቤት መጥሪያ ከነ ጋዎናቸዉ ጭምር ወደ ሀንጣጤ ፖሊስ ጣቢያ አስገብተዋቸዋል " ሲሉ ገልፀዋል።
" ሁሉም የሆስፒታሉ ሠራተኞች አንድ ላይ በመሆን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ብንሄድም ' ከበላይ አካላት ታዘን ነዉ ' የሚል ምላሽ ነዉ የተሰጠን " ብለዋል።
ሠራተኞቹ ቀኑን ሙሉ እዛዉ ለመሆን መወሰናቸዉንና ከአስራ አንድ ሰዓት በኋላ የተወሰኑ አመራሮች ወደ ፖሊስ ጣቢያ የመጡ ቢሆንም የታሰሩት ሳይፈቱ ወደ ' ቤታችሁ ሂዱ ' ተብለው እስኪጨላልም እዛዉ የቀሩ ባለሙያዎች እንደነበሩ አስረድተዋል።
" የትርፍ ሰዓት ክፍያ ካልተከፈለን ብለን ስራ አላቆምን " የሚሉት የጤና ባለሙያዎቹ " አይደለም መደበኛ ስራ ለማቆም ምንም ሳይከፈለን በብዙ ችግሮች ዉስጥ ሆነን እራሳችንን እየጎዳን ከ8 ወራት በላይ የትርፍ ሰዓቱን ስራ ጭምር ስንሰራ ቆይተናል ነገሮች ከአቅማችን በላይ ሲሆኑ በደብዳቤ አሳዉቀን የትርፍ ሰዓቱን ስራ ለማቆም ተገደናል " ብለዋል።
ሁሉም ሠራተኛ የትርፍ ሰዓት ስራ ባቆመበት ሁኔታ የሆስፒታሉን ሜዲካል ዳይሬክተር ጨምሮ የማኔጅመንት አባላትንና የተወሰኑ ሠራተኞችን ለይቶ የማሰሩ ጉዳይ ተገብነት የሌለው እና የሚመለከታቸዉ አካላት በአፋጣኝ እልባት ሊሰጡበት የሚገባ ጉዳይ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
" ' ሚዲያ ላይ ስለከሰሳችሁ ሚዲያ የሚከፍላችሁ መስሏችኋል' የሚሉ አመራሮች ነበሩ " ያሉን ቅሬታ አቅራቢዎቹ " ሜዲካል ዳይሬክተሩንና ማኔጅመንቱን ' ለምን ሠራተኛ ታሳምፃላችሁ፣ ከወረዳዉና ከዞኑ መንግስት የሚተላለፍላችሁን መመሪያ ለምን አታስፈፅሙም ' ብለዉ የሚያስፈራሩም ነበሩ " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የከፍተኛ አመራሮችን ምላሽ ለማግኘት ጥረት አድርጓል።
ከዚህ ቀደም የማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መንግስቱ ማቴዎስ በስልክ መረጃ የሰጡን ቢሆንም አሁን ላይ " ወደ ቦታዉ በአካል ካልመጣችሁ መረጃ መስጠት አልችልም " በማለታቸዉ ሳይሳካ ቀርቷል።
ፈቃደኛ ሲሆኑ ምላሻቸዉን የምናካትት ይሆናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
@tikvahethiopia
#የጤናባለሙያዎችድምጽ
" የሆስፒታሉን ሜዲካል ዳይሬክተር ጨምሮ 14 የሚሆኑ የጤና ባለሙያዎች እና አስተዳደር ሰራተኞች ከስራ ቦታቸዉ ተወስደው ታስረዋል " - የሀንጣጤ ሆስፒታል ባለሙያዎች
" ' ለሚዲያ መረጃ ስለሰጣችሁ ሚዲያ የሚከፍላችሁ መስሏችኋል ' የሚሉ አመራሮችም አሉ ! "
በሲዳማ ክልል፤ ማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ሎካ አባያ ወረዳ በሚገኘዉ ሀንጣጤ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል የሚሰሩ የጤና ባለሙያዎች ከ8 ወራት በላይ የትርፍ ሰዓት ክፊያ ባለመከፈሉ ለሎካ አባያ ወረዳ፣ ለማዕከላዊ ሲዳማ ዞንና ለሲዳማ ክልል ጤና ቢሮ በደብዳቤ ካሳወቁ በኋላ የትርፍ ሰዓት ስራ ማቆማቸዉን ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ከዚህ ቀደም ማሳወቃቸው ይታወሳል።
በወቅቱ ስለ ጉዳዩ ምላሽና ማብራሪያ የሰጡት የማዕከላዊ ሲዳማ ዞን አስተዳዳሪ አቶ መንግስቱ ማቴዎስ ፥ የሠራተኛዉ ጥያቄ ትክክለኛ መሆኑን ገልፀዉ ክፍያዉ እንዲፈፀም ከክልሉ መንግስት ብድር መጠየቃቸዉንና በቅርቡ እንደሚከፈላቸዉ ገልፀዉ የነበረ ሲሆን " የትርፍ ሰዓት ስራ ማቆም መብታቸዉ ነዉ " ሲሉ ገልጸውም ነበር።
ትላንት የሆስፒታሉ ሠራተኞች ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት " ሁሉም ሰራተኛ በአንድነት ተፈራርሞ ባስገባዉ ደብዳቤ መሰረት ከባለፈዉ ሳምንት ጀምሮ የትርፍ ሰዓት ስራ ብቻ ያቆሙ ቢሆንም የሆስፒታሉን ሜዲካል ዳይሬክር እና 7 የማኔጀመንት አካላትን ጨምሮ 14 የሚሆኑ የሆስፒታሉ ባለሙያዎችን ፖሊስ ከስራ ቦታቸዉ ጭምር ወስዶ አስሯቸዋል " ብለዋል።
" ሁሉም ሠራተኛ የትርፍ ሰዓት ስራ ማቆሙ ሰበብ ተደርጎ በመደበኛ ስራዉ ላይ እንከን እንዳይፈለግበትና ላለመከሰስ የስራ ሰዓቱን በአግባቡ እየተጠቀመ ነዉ " የሚሉት ሠራተኞቹ " ትላንት ጠዋት በድንገት 2 ዶክተሮች፣ 7 ነርሶችንና ሌሎች ባለሙያዎችን 'ትፈለጋላችሁ' በሚል ያለ ፍርድ ቤት መጥሪያ ከነ ጋዎናቸዉ ጭምር ወደ ሀንጣጤ ፖሊስ ጣቢያ አስገብተዋቸዋል " ሲሉ ገልፀዋል።
" ሁሉም የሆስፒታሉ ሠራተኞች አንድ ላይ በመሆን ወደ ፖሊስ ጣቢያ ብንሄድም ' ከበላይ አካላት ታዘን ነዉ ' የሚል ምላሽ ነዉ የተሰጠን " ብለዋል።
ሠራተኞቹ ቀኑን ሙሉ እዛዉ ለመሆን መወሰናቸዉንና ከአስራ አንድ ሰዓት በኋላ የተወሰኑ አመራሮች ወደ ፖሊስ ጣቢያ የመጡ ቢሆንም የታሰሩት ሳይፈቱ ወደ ' ቤታችሁ ሂዱ ' ተብለው እስኪጨላልም እዛዉ የቀሩ ባለሙያዎች እንደነበሩ አስረድተዋል።
" የትርፍ ሰዓት ክፍያ ካልተከፈለን ብለን ስራ አላቆምን " የሚሉት የጤና ባለሙያዎቹ " አይደለም መደበኛ ስራ ለማቆም ምንም ሳይከፈለን በብዙ ችግሮች ዉስጥ ሆነን እራሳችንን እየጎዳን ከ8 ወራት በላይ የትርፍ ሰዓቱን ስራ ጭምር ስንሰራ ቆይተናል ነገሮች ከአቅማችን በላይ ሲሆኑ በደብዳቤ አሳዉቀን የትርፍ ሰዓቱን ስራ ለማቆም ተገደናል " ብለዋል።
ሁሉም ሠራተኛ የትርፍ ሰዓት ስራ ባቆመበት ሁኔታ የሆስፒታሉን ሜዲካል ዳይሬክተር ጨምሮ የማኔጅመንት አባላትንና የተወሰኑ ሠራተኞችን ለይቶ የማሰሩ ጉዳይ ተገብነት የሌለው እና የሚመለከታቸዉ አካላት በአፋጣኝ እልባት ሊሰጡበት የሚገባ ጉዳይ ስለመሆኑ ገልጸዋል።
" ' ሚዲያ ላይ ስለከሰሳችሁ ሚዲያ የሚከፍላችሁ መስሏችኋል' የሚሉ አመራሮች ነበሩ " ያሉን ቅሬታ አቅራቢዎቹ " ሜዲካል ዳይሬክተሩንና ማኔጅመንቱን ' ለምን ሠራተኛ ታሳምፃላችሁ፣ ከወረዳዉና ከዞኑ መንግስት የሚተላለፍላችሁን መመሪያ ለምን አታስፈፅሙም ' ብለዉ የሚያስፈራሩም ነበሩ " ሲሉ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ አስታዉቀዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የከፍተኛ አመራሮችን ምላሽ ለማግኘት ጥረት አድርጓል።
ከዚህ ቀደም የማዕከላዊ ሲዳማ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ መንግስቱ ማቴዎስ በስልክ መረጃ የሰጡን ቢሆንም አሁን ላይ " ወደ ቦታዉ በአካል ካልመጣችሁ መረጃ መስጠት አልችልም " በማለታቸዉ ሳይሳካ ቀርቷል።
ፈቃደኛ ሲሆኑ ምላሻቸዉን የምናካትት ይሆናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
ሀዋሳ
@tikvahethiopia
😭500😡222❤55😢29🙏10🥰8🤔7👏5🕊5
TIKVAH-ETHIOPIA
“ በሙያው ጠቅላላ ሀኪም ነው ቤተሰብ ለመጠየቅ እየሄደ ነው በጥይት ተመትቶ የተገደለው ” - የሟች ጓደኛ በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን መራቢቴ ወረዳ በእናት ሆስፒታል የጠቅላላ ህክምና ሀኪሙ “በተተኮሰበት ጥይት” መገደሉን የቅርብ ሰዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጹ። ዶክተር ገብረሚካኤል ወልደ መላክ ተገደለ የተባለው ቤተሰቦቹን ለመጠየቅ በመኪና እየተጓዘ መራቢቴ አካባቢ መሆኑን ገልጸዋል። ቃላቸውን የሰጡን…
“ ጤና ባለሙያዎች ላይ እየደረሰ ያለው የግድያ ወንጀል ከቀን ወደ ቀን አሳሳቢ እየሆነ ነው ” - ማኀበሩ
በደመወዝ ከመበደላቸው በባሰ ሁኔታ ጤና ባለሙያዎች ላይ የሚፈጸሙ ግድያዎች እየተሰባባሱና አሳሳቢ እየሆኑ መምጣታቸውን የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኀበር ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ገለጸ።
የማኀበሩ ፕሬዚደንት አቶ ዮናታን ዳኛው በሰጡን ቃል፣ “ ጤና ባለሙያዎች ላይ እየደረሰ ያለው የግድያ ወንጀል ከቀን ወደ ቀን አሳሳቢ እየሆነ ነው ” ብለዋል።
የማኀበሩ ፕሬዚደንት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
“ የሀገርን ስብራት የሚጠግኑ ጤና ባለሙያዎችን፣ ሀኪሞችን መግደል የትውልድን የነገ ተስፋ ማጨለም ነው። በኢትዮጵያ ሀኪሞች ተገደሉ ሚለው መርዶ ከመደጋገሙ የተነሳ የዘወትር ዜና ሆኗል።
ብዙ ዋጋ ከፍለው የሰውን ሕይወት የሚታደጉ፣ ችግሮችን ተጋፍጠው የተቀማን ህልም የሚያለመልሙ ሀኪሞች ለምን ይገደላሉ?
እድሜያቸው ለጋ የሆነ፣ ሀገርን ብዙ የሚያገለግሉ፣ ሀገር ብዙ የደከመችባቸውን ሀኪሞች መግደል የሀገርን የነገ እጣ ፈንታ የሚያበላሽ አሳፋሪ ተግባር በመሆኑ ሁሉም ዜጋ በእኩል ሊያወግዘውና ሊታገለው ይገባል።
መንግስት ጤና ባለሙያዎች የሚሰሩበትን አካባቢ ከየትኛውም አደጋ ነፃ መሆኑን ማረጋገጥና ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠርን ቀዳሚ ተግባሩ አድርጎ ሊሰራ ይገባል።
አብዛኞቹ ጤና ተቋማት ደህንነታቸው በበቂ ሁኔታ የተጠበቀ አለመሆኑ ደግሞ ጉዳዩን የበለጠ ውስብስብ ያደርገዋል።
በገቡት ቃል ኪዳን መሰረት ሁሉንም ዜጋ ያለ ምንም ልዩነት ሚያገለግሉ፣ የፓለቲካ ውግንና የሌላቸው ጤና ባለሙያዎችን ያነጣጠር የግድያ ወንጀል በምንም መመዘኛ ተቀባይነት የለውም።
በአስቸኳይ እልባት ይሻል ” ነው ያሉት።
ከቀናት በፊት መራቢቴ ወረዳ በእናት ሆስፒታል የጠቅላላ ህክምና ሀኪም የነበረው ዶክተር ገብረሚካኤል ወልደ መላክ ቤተሰብ ጥየቃ በመኪና እየሄደ በነበረበት ወቅት “ በተተኮሰበት ጥይት ” መገደሉን የቅርብ ሰዎቹ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ መግለጻቸው ይታወሳል።
ከወራት በፊት ደግሞ የባሕርዳር ዩኒቨርሲቲ ህክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የጥበበ ግዮን ግቢ ስፔሻላንስድ ሆስፒታል የቀዶ ህክምና አገልግሎት ክፍል ዳይሬክተር ዶክተር አንዷለም ዳኘ በተተኮሰባቸው ጥይት መገዳላቸው አይዘነጋም።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
😭994💔112❤84😢33😡24🕊17🥰8🤔8😱7
" አስተዳደራዊ በደል በድሬዳዋ ጤና ቢሮ ተፈፅሞብኛል " - የሳቢያን ሆስፒታል ሀኪም ዶክተር ሀብታሙ አለሙ
➡️ " በሆስፒታሉ ከተቀጠረ ጀምሮ እስካሁን ድረስ የቀረበበት የዲስፕሊን ጉድለት የለም " - የሳቢያን ሆስፒታል የዲሲፕሊን ኮሚቴ
በድሬዳዋ አስተዳደር ጤና ቢሮ ሳቢያን ሆስፒታል የጠቅላላ ህክምና ሃኪም የሆኑት ዶክተር ሀብታሙ አለሙ በሀገር አቀፍ ደረጃ የህክምና ባለሙያዎች ያቀረቡትን ቅሬታ በመደገፋቸው በቢሮው አስተዳደራዊ በደል ተፈፅሞብኛል በማለት ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ቅሬታቸውን አቅርበዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተውና ለባለሞያው የተጻፈው ደብዳቤ " ለስራ በተመደበበት ክፍል የሙያ ስነምግባርን በተፃረረ መልኩ በእናቶች እና በህፃናት ክፍል ወላድ እናቶችን በተደጋጋሚ ማመናጨቅ፣ መሳደብ እና ያለአግባብ ማመላለስ እና ማስጠንቀቂያ ቢሰጥም ባለመታረሙ ወደ ገኦዳ ጉዱንፈታ ጤና ጣቢያ አዘዋውረናል " የሚል ነው።
የጤና ባለሙያው ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ምን አሉ ?
" በሀገር አቀፍ ደረጃ የህክምና ባለሙያዎች የደመወዝ ጭማሪ ይደረግልን ተብሎ ቅሬታ ሲያቀርቡ ለምን ሃሳቡን ደገፍክ ብለው የድሬዳዋ ከተማ ጤና ቢሮ ሃላፊ እና ምክትል ደውለው ለምን ይሄን አደረክ አሉኝ፣ እኔም ጥያቄው እንደሀገር ነው የቀረበው፣ እንደ ድሬዳዋ አይደለም፣ ይሄ ደግሞ የመብት ጥያቄ ነው ብየ መለስኩኝ ።
የሃላፋዎች ምላሽም በድሬዳዋ ከተማ አንደዚህ መንቀሳቀስ አትችሉም፣ የከተማችንን ስም ያቆሽሽብናል፣ ስለዚህ የህክምና ባለሙያው ዝም ነው ማለት ያለበት አሉኝ።
በነጋታው ከሰዓት የዝውውር ደብዳቤ እና የዲስፕሊን ጉድለት አለብህ ብለው ከሃላፊዎች ሲሰጠኝ የጤና ቢሮ ሃላፊዋን ዶክተር ፅጌሬዳን ለማናገር ቢሮ ስሄድ ባለማግኜቴ ስልክ በመደወል ሳናግሯቸው ቅድሚያ ስሜን አጥፍተሀል እና ፌስቡክ ላይ ይቅርታ ብለህ ፃፍ ከዚያ ውጭ አላናግርህም አሉኝ " ሲሉ አስረድተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ በዚህ ላይ ስማቸው የተጠቀሰው የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ኃላፊ ዶ/ር ጽጌረዳ ክፍሌ እንዲሁም ምክትል ኃላፊ አቶ ዩሱፍ ሰይድ ለማነጋገር በተደጋጋሚ ስልካቸው ላይ ቢደውልም ምላሽ ማግኘት አልቻልም።
በጉዳዩ ላይ የሳቢያን ሆስፒታል የዲሲፕሊን ኮሚቴ ምን አለ ?
ዶ/ር ሀብታሙ " እንደ ሆስፒታል በዲስፕሊን ተፅፎብኝ የሚያውቅ ደብዳቤ የለም " ማለታቸውን ተከትሎ ቲክቫህ ኢትዮጵያ የሳቢያን ሆስፒታል የዲሲፕሊን ኮሚቴ ሰብሳቢ የሆኑትን ዶክተር አባይነህን ጠይቋል።
በምላሻቸውም " በሆስፒታሉ ከተቀጠረ ጀምሮ እስካሁን ድረስ የቀረበበት የዲስፕሊን ጉድለት ክስ #የለም " ሲሉ ማረጋገጫ ሰጥተዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ይህንን መረጃ እያዘጋጀ በነበረበት ወቅት የሆስፒታሉ ስራ አስኪያጅ ሲስተር መስከረም አሰፋ በኃላፊነት ቦታቸው ላይ እንደሌሉ ሰምቷል።
ሲስተር መስከረም ይኽ መረጃ እስከተዘጋጀበት ጊዜ ከሥራ እረፍት እንዲያደርጉ እንጂ ዝውውርም ሆነ እድገት እንዳልተሰጣቸው ለማረጋገጥ ችለናል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከደመወዝ ጥያቄው ጋር በተገናኘ እንዲሁም በዚህ መረጃ ላይ ለቀረቡት ቅሬታዎች የድሬዳዋ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ ሃላፊዎችን ለማናገር ያደረግው ጥረት ባለመሳካቱ ምላሻቸውን ማካተት ሳይቻል ቀርቷል።
በጉዳዩ ላይ ቢሮውም ሆነ ማንኛውም አካል ምላሽ እና ማብራሪያ ለመስጠት ፈቃደኛ ከሆነ ለማስተናገድ ዝግጁ መሆኑን ይገልጻል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
አዲስ አበባ
#TikvahEthiopia
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
😭911😡166❤128💔33🤔23😢20🥰10🕊10👏8🙏8😱5
TIKVAH-ETHIOPIA
“ መጀመሪያ እየሰራሁ ወደነበረበት ሳቢያን ሆስፒታል ተመልሸ ስራዬን እንድቀጥል ይደረግልኝ ” - የጠቅላላ ሀኪሙ ዶ/ር ሀብታሙ አለሙ
• “ የዝውውር ዓላማ ክፍት ቦታ ሲኖር ሥራንና ሠራተኞቸን ማገናኘት ነው እንጂ ዝውውር የቅጣት ውጤት አይደለም ” - ማኀበሩ
በድሬዳዋ ሳቢያን ጠቅላላ ሆስፒታል የጠቅላላ ሀኪም ዶክተር ሀብታሙ አለሙ ደረሰብኝ ላሉት በደል ፍትህ እንዲያሰጣቸው በኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኀበር በኩል በደብዳቤ አቤት ብለዋል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ የተመለከተው የአቤቱታ ደብዳቤያቸው ምን ይላል ?
በጠቅላላ ሀኪምነት ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከተመረቁ በኋላ ወዳስተማረቻቸውና ያሳደገቻቸው ድሬዳዋ ከተማ ለሦስት ወራት የነፃ አገልግሎት እንደሰጡ ይገልጻል።
በኋላም በአስተዳደሩ በወጣ ማስታወቂያ ወድድር አልፈው በ2016 ዓ/ም በሆስፒታሉ በትጋትና ከፍተኛ ፍቅር ህብዝን ሲያገለግሉ እንደነበር ያስረዳል።
ከሰሞኑን እንደ ሀገር በተጀመሩ የጤና ባለሙያዎች የመብት ጥያቄዎች ሰላማዊ እንቅስቃሴ በፅሑፍ ያላቸውን ተሰሚነት በመጠቀም ሌሎችን በማንቃት ሲሳተፉ የጤና ቢሮው ኃላፊዎች ከዚህ እንዲታቀቡ ቢያስጠነቅቋቸውም የመብት ጥያቄ ማንሳት እንደማያቆሙ ማሳወቃቸውን ይጠቅሳል።
ይህን ባሳወቁ ማግስትም (ማክሰኞ ሚያዚያ 14/2017 ዓ/ም) በተፃፈላቸው ደብዳቤ ጥፋት እንዳለባቸው ተገልጾ የሥራ ቦታ እንዲቀይሩ መደረጋደቸውን ያትታል።
ሀኪሙ ይህንኑ እርምጃ፣ “ ህገ ወጥና ስርዓቱን ያልተከተለ በቂም በቀል የተጻፈ ደብዴቤ አግባብ አለመሆኑ እና የሥም ማጥፋት መሆኑን ” ገልጸው፣ ውሳኔው ተቀልብሶ ሲሰሩበት ወደነበረው ሳቢያን ሆስፒታል እንዲመለሱ እንዲደረግላቸው የኢትዮጵያ ጤና ባለሙያዎች ማኀበርን በደብዳቤ ጠይቀዋል።
ማኀበሩ ለድሬዳዋ ጤና ቢሮ የጻፈው ደብዳቤስ ምን ይላል ?
ሀኪሙ ወደ ሌላ ጣቢያ እንዲዘዋወሩ መደረጋቸውን ገልጾ፣ “በፌደራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ መሠረት የዝውውር ዋና ዓላማ ክፍት ቦታ ሲኖር ሥራንና ሠራተኞቸን ማገናኘት ነው እንጂ ዝውውር የቅጣት ውጤት አይደለም” ብሏል።
ይሁን እንጂ ለሠራተኛው የውስጥ ዝውውር ምክንያቱ " የዲስፕሊን ችግር " መባሉን ጠቅሶ፣ በሀኪሙ ላይ በመረጃ የተደገፈ የዲሲፕሊን ግድፈት ባለመኖሩ ወደ ስራ ቦታቸው እንዲመለሱ ሲል ቢሮውን ጠይቋል።
(የሀኪሙና የማኅበሩ ደብዳቤዎች ከላይ ተያይዘዋል)
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
❤912😭196🙏83👏67🕊19🤔12😢11💔8😱7😡4🥰3