TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.2K photos
1.62K videos
218 files
4.4K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update #Axum

የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት በሰጠው ማሳሰቢያ ፥ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ምዝገባ ዛሬ ጥር 6/2017 ዓ.ም ከቀኑ 11፡00 ሰዓት ላይ ተጠናቋል።

" ያልተመዘገበ አይፈተንም " ማለቱ ይታወሳል።

ከሙስሊም ተማሪዎች ሂጃብ መልበስ ጋር ተያይዞ በአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የተነሳው ውዝግብ ባለመግባባት ተቋጭቷል።

159 የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል አገር አገር አቀፍ ፈተና ለማሳተፍ የሚያስችላቸው ፎርም ሳይሞሉ የተሰጠው የምዝገበ ቀነ ገደብ ዛሬ አልቋል።

ጉዳዩን በቅርበት ሲከታተለው የቆየው ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ዛሬ ጥር 6 ቀን 2017 ከሰዓት በኋላ ወደ አክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ርእሰ መምህር  ስዩም ካሕሳይ ደውሎ አግኝቷቸዋል።

ርእሰ መምህር ስዩም ካሕሳይ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ በሰጡት ቃል ምን አሉ ?

" - በትምህርት ቤታችን ከተለመደው የአለባበስ ስርዓት የተለየ የተሰጠ የአለባበስ ትእዛዝ የለም።

- ሴት ሙስሊም ተማሪዎቻችን እስከ ዛሬዋ ቀን ድረስ ከትምህርት ቤቱ አመራር በአካል በመምጣት እንዲወያዩ ማስታወቅያ በመለጠፍና ስልክ በመደወል ጥረት ተደርጓል ለመምጣት ፍቃደኛ ኣይደሉም።

- የአክሱም ከተማ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት አመራሮች ጉዳዩ እንዲረግብ ከትምህርት ቤታችን ፣ ከከተማዋ ከንቲባ ከአገር ሽማግሌ እና ከክልል ትምህርት ቢሮ ሰላማዊ ልመና ቢቅርብላቸውም ጉዳዩ ለማርገብ ፍቃደኛ አልሆኑም።

- በአጠቃላይ የፈተና ፎርም ያለ መሙላትና ያለ መፈተን ፍላጎቱ ከተማሪዎቻች ፍላጎት ውጪ የውጭ ተፅእኖ እና ግፊት አለበት።

- ልጆቻችን በቀላሉ በመግባባት ሊፈታ በሚችል ጉዳይ ከፈተና ውጪ መሆናቸው እንደ ርእሰ መምህርና ወላጅ እጅግ እሞኛል አበሳጭቶኛል " ... ብለዋል።

የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ታህሳስ 22 ቀን 2017 ከህገ-መግስት ከሃይማኖታዊ ስርዓት ክልከላ ውጪ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች " ሂጃብ " እንዳይለብሱ ስለተደረገው ክልከላ እና የመብት ጥሰት አስመልክቶ ባወጣው ባለ 11 ነጥብ የአቋም መግለጫ  ፥ " ፍትሃዊ ጥያቄያችን በሦስት ቀናት ውስጥ ካልተፈታ የክልላችን የእስልምና ጉዳዮች ም/ቤት ከህዝበ ሙስሊሙ ጋር በመምከር በቀጣይ የምንወስዳቸው ሰላማዊ የትግል እርምጃዎችን ለህዝባችን እናሳውቃለን " ማለቱ ይታወሳል። 

ም/ቤቱ ባወጣው መግለጫ መሰረት ጥያቄዎቹ በሚመለከተው አካል ጀሮ ዳባ ልበስ መባላቸውን በማረጋገጡ በታህሳስ 30 ቀን 2017 ባወጣው አጭር መግለጫ ጉዳዩ በህግ እንዲታይ ክስ መመስረቱ ግልጽ አድርጓል። 

ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ም/ቤት አመራሮች ስለ ጉዳዩ አሁናዊ ሁኔታ ተጨማሪ ማብራርያ እንዲሰጡ ጥር 6/2017 ዓ.ም ከሰዓት በኋላ ያደረገው ሙከራ ለጊዜው አልተሳካም።

ከ2017 ዓ/ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ውጭ የሆኑት 159 የአክሱም ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ጉዳይ ወዴት ያመራ ይሆን ? ቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ ጉዳዩ ተከታትሎ ያቀርባል።

@tikvahethiopia
2😡1.08K188😢71👏66😭57🕊35🤔26🙏26🥰11😱6💔1
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የትግራይ ማእከላይ ዞን ፍርድ ቤት የአክሱም ከተማ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከነሂጃባቸው እንዲማሩ ወሰነ። የወረዳ ፍርድ ቤት በትግራይ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ላይ ያስቀመጠው የገንዘብ መቀጮም እንዲቀር ወስኗል። የትግራይ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት መጋቢት 30/2017 ዓ.ም በይፋዊ የማህበራዊ የትስስር ገፁ እንዳሰፈረው ፤ ከአሁን በፊት በአክሱም ከተማ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች…
#Axum

" የአክሱም ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ሂጃብ በመልበሳቸው ምክንያት የ12ኛ ክፍል ፈተናን እንዳይወስዱ ተደርገዋል " - የሙስሊም ሴት ተማሪዎችን ጉዳይ የሚከታተሉ አካላት

➡️ " ፈተና ማእከል ደርሳ ሂጃብ በመልበስዋ ምክንያት የተባረረች እንዲት ሙስሊም ተማሪ የለችም ፤ የፈጠራ ወሬና ጥላሸት መቀባት ይቁም " - የትምህርት ቢሮ ሃላፊ


የአክሱም ከተማ ሴት ተማሪዎች የሂጃብ መልበስ ክልከላ ጋር ተያይዞ የተነሳው ውዝግብ ወራትን አስቆጥሯል።

ዛሬ በአገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ፈተና ሲጀመር የአክሱም ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ጉዳይ ተነስቷል።

የሙስሊም ሴት ተማሪዎችን ጉዳይ የሚከታተሉ አካላት ፥ " የአክሱም ከተማ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች በሂጃብ ክልከላ ምክንያት የ12ኛ ክፍል ፈተናን እንዳይወስዱ ተደርገዋል " በማለት አስተያየታቸውን በማህበራዊ የትስስር ገፆች አሰራጭተዋል።

" ሂጃብ ከመልበስ ጋር ተያይዞ እንዲት ሙስሊም ተማሪ ከፈተና ማእከል የተባረረች የለችም " በማለት ለተሰራጩት ፅሁፎችና አስተያየቶች ምላሽ የሰጡት የክልሉ ትምህርት ቢሮ ሃላፊ ኪሮስ ጉዕሽ (ዶ/ር)  " ፈተና ለመውሰድ የተመዘገቡት 24 ሴት ተማሪዎች በራሳቸው ፍላጎት ሳይመጡ ቀርተዋል " ብለዋል። 

" ሴት ሙስሊም ተማሪዎቹ  የመፈተን ፍላጎት ካላቸው ሀሙስ ሰኔ 26/2017 ዓ.ም በሚጀመረው ሁለተኛ ዙር ፈተና መፈተን ይችላሉ ፤ ከዚህ ውጪ ተማሪዎቹ እንዳይፈተኑ በመከልከል ሆን ተብሎ የሚፈጠረው የማጠልሽት ተግባርና ውሸት ለህዝብና አገር አይጠቅምም " በማለት አክለዋል።

ዛሬ በተጀመረው የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና 36 ሺህ ተማሪዎች ፈተናውን መውሰድ ጀምረዋል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMekelle

@tikvahethiopia            
41.66K😡668💔205😭141👏105🕊60🤔55🙏30🥰28😢25😱24
#Axum

የአክሱም ከተማ ፖሊስ በከተማው ክንደያ በተባለ ቀበሌ ሁለት ተጠርጣሪዎች አደገኛ ኬሚካል በመጠቀም የወርቅ ማጣራት ተግባር ሲያከናውኑ በቁጥጥር ስር እንዳዋላቸው አሳውቋል።

ፖሊስ ከህብረተሰብ በደረሰው ጥቆማ የፍ/ቤት የፍተሻ ትእዛዝ በመያዝ የተለያዩ የፍትህ አካላት ፣ የአገር ሽማግሌዎችና የጤና ባለሙያዎች በማሳተፍ ነው ተጠርጣሪዎች በቁጥጥር ስር ያዋላቸው፡፡

የከተማዋ አቃቤ ህግ የህበረተሰብ የጤና ጠንቅ የሆነውን አደገኛ ኬሚካል በመጠቀም ህገወጥ ተግባር ሲፈፅሙ የተገኙት ተጠርጣሪዎቹ በአጭር ጊዜ አስተማሪ ቅጣት እንዲያገኙ ከባለ ድርሻ አካላት በመሆን ይሰራል ብሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ

Photo credit - Tigrai Television

@tikvahethiopia
400👏47🤔18🙏12😡12🕊6😭6😱1