TIKVAH-ETHIOPIA
#USA #China ቻይና በአሜሪካ ላይ አፀፋዊ የሆነ ተጨማሪ ታሪፍ ጥላለች። ቻይና ከዚህ በፊት ከአሜሪካ በሚገቡ ምርቶች ላይ የ84% ታሪፍ ጥላ የነበረ ሲሆን ዛሬ ሌላ ተጨማሪ ታሪፍ ጥላለች። የቻይና የፋይናንስ ሚኒስትር ከአሜሪካ በሚገቡ ዕቃዎች ላይ የተጣለው ታሪፍ ከ84% ወደ 125% ከፍ መደረጉን አስታውቀዋል። የትራምፕ አስተዳደር በቻይና ላይ የተጣለው አጠቃላይ ታሪፍ 145% መሆኑን የገለፀ…
#USA #CHINA
የአሜሪካ እና የቻይና የታሪፍ ጦርነት !
ወደ አሜሪካ የሚገቡ የኤሌክትሮኒክስ ምርቶች ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ ከጣሏቸው የአፀፋ ታሪፎች ነፃ መሆናቸውን የአሜሪካ የጉምሩክ ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል።
➡️ ስማርት ስልኮች፣
➡️ ኮምፒዩተሮች
➡️ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ክፍሎች ትራምፕ ከጣሉት ታሪፍ ነፃ መደረጋቸውም ተዘግቧል።
ውሳኔው የመጣው የፕሬዚዳንት ትራምፕ አስተዳደር በቻይና ላይ የ145% አጠቃላይ ታሪፍ መጣሉን ካስታወቀ በኋላ ሲሆን የታሪፉ መጣል እንደ አፕል ላሉ ግዙፍ የኤሌክትሮኒክ ምርት አምራቾች ስጋትን ፈጥሮም ነበር።
አፕል 90% የሚሆነውን የአይፎን ስልክ የሚያመርተው እና የሚገጣጥመው በቻይና ሲሆን ካውንተር ፖይንት የተሰኘው የጥናት ተቋም አፕል በአሜሪካ ያለው ክምችት ለ6 ሳምንታት ብቻ የሚሆን እንደሆነና እሱ ካለቀ የምርቱ ዋጋ መጨመር እንደሚጀምር ገልጾ ነበር።
አፕል ከአይፎን በተጨማሪ 80% የሚሆነውን አይፓድ እና ከ50% በላይ የሚሆነውን የማክ ኮምፒዩተር ምርቶቹን በቻይና እንደሚያመርት ተገልጿል።
አፕል ከግማሽ በመቶ በላይ የሚሆነውን የአይፎን ምርት የሚሸጠው በአሜሪካ እንደሆነ ሲነገር በቻይና ላይ ታሪፍ መጣሉን ተከትሎ አብዛኛውን ምርቱን በህንድ ማምረት ለመጀመር ማሰቡም ተነግሮ ነበር።
አፕል ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአፀፋ ታሪፍ በሃገራት ላይ መጣል ከጀመሩ በኋላ የገበያ ዋጋው በ640 ቢሊየን ዶላር መቀነሱ የተዘገበ ሲሆን ከ600 ቶን በላይ ክብደት ያላቸው 1.5 ሚሊየን የአይፎን ስልኮችንም ከህንድ ወደ አሜሪካ በአውሮፕላን አጓጉዞ ማስገባቱ መዘገቡ ይታወሳል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትናንትና አንዳንድ ምርቶች በሚታወቁ ምክንያቶች እሳቸው ከጣሉት ታሪፍ ነፃ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተናግረው ነበር።
ትራምፕ በጣሉት ታሪፍ የተነሳ የአይፎን ስልክ ዋጋ በሶስት እጥፍ ሊጨምር እንደሚችል ስጋቶች የነበሩ ቢሆንም አሁን ላይ የኤሌክትሮኒክስ ምርቶቹ ከአፀፋዊ ታሪፉ ነፃ መሆን ትልቅ ዕድል እንደሚሆን ተዘግቧል።
በውሳኔው መሰረትም #ሳምሰንግን ጨምሮ ሌሎች አለም አቀፍ የኤሌክትሮኒክስ አምራቾች ወደ አሜሪካ ምርታቸውን ሲልኩ ይጠብቃቸው ከነበረው የ10% መሰረታዊ ታሪፍም ነፃ መሆናቸው ተነግሯል።
ከታሪፉ ነፃ የሆኑ 20 የምርት ዘርፎች የተቀመጡ ሲሆን ለሴሚ ኮንዳክተር መሳሪያነት የሚያገለግሉ ማሽኖችም ከታሪፉ ነፃ መሆናቸው ታውቋል።
ኋይት ሃውስ፣ የአሜሪካ የአለም አቀፍ ንግዶች ኮሚሽን እና የአሜሪካ የንግድ ቢሮ በጉዳዩ ላይ እስካሁን አስተያየት አልሰጡም።
#ዓለምአቀፍ #የታሪፍጦርነት #ቻይና #አሜሪካ
@tikvahethiopia
የአሜሪካ እና የቻይና የታሪፍ ጦርነት !
ወደ አሜሪካ የሚገቡ የኤሌክትሮኒክስ ምርቶች ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በቅርቡ ከጣሏቸው የአፀፋ ታሪፎች ነፃ መሆናቸውን የአሜሪካ የጉምሩክ ጉዳዮች ቢሮ አስታውቋል።
➡️ ስማርት ስልኮች፣
➡️ ኮምፒዩተሮች
➡️ የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ ክፍሎች ትራምፕ ከጣሉት ታሪፍ ነፃ መደረጋቸውም ተዘግቧል።
ውሳኔው የመጣው የፕሬዚዳንት ትራምፕ አስተዳደር በቻይና ላይ የ145% አጠቃላይ ታሪፍ መጣሉን ካስታወቀ በኋላ ሲሆን የታሪፉ መጣል እንደ አፕል ላሉ ግዙፍ የኤሌክትሮኒክ ምርት አምራቾች ስጋትን ፈጥሮም ነበር።
አፕል 90% የሚሆነውን የአይፎን ስልክ የሚያመርተው እና የሚገጣጥመው በቻይና ሲሆን ካውንተር ፖይንት የተሰኘው የጥናት ተቋም አፕል በአሜሪካ ያለው ክምችት ለ6 ሳምንታት ብቻ የሚሆን እንደሆነና እሱ ካለቀ የምርቱ ዋጋ መጨመር እንደሚጀምር ገልጾ ነበር።
አፕል ከአይፎን በተጨማሪ 80% የሚሆነውን አይፓድ እና ከ50% በላይ የሚሆነውን የማክ ኮምፒዩተር ምርቶቹን በቻይና እንደሚያመርት ተገልጿል።
አፕል ከግማሽ በመቶ በላይ የሚሆነውን የአይፎን ምርት የሚሸጠው በአሜሪካ እንደሆነ ሲነገር በቻይና ላይ ታሪፍ መጣሉን ተከትሎ አብዛኛውን ምርቱን በህንድ ማምረት ለመጀመር ማሰቡም ተነግሮ ነበር።
አፕል ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአፀፋ ታሪፍ በሃገራት ላይ መጣል ከጀመሩ በኋላ የገበያ ዋጋው በ640 ቢሊየን ዶላር መቀነሱ የተዘገበ ሲሆን ከ600 ቶን በላይ ክብደት ያላቸው 1.5 ሚሊየን የአይፎን ስልኮችንም ከህንድ ወደ አሜሪካ በአውሮፕላን አጓጉዞ ማስገባቱ መዘገቡ ይታወሳል።
ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትናንትና አንዳንድ ምርቶች በሚታወቁ ምክንያቶች እሳቸው ከጣሉት ታሪፍ ነፃ ሊሆኑ እንደሚችሉ ተናግረው ነበር።
ትራምፕ በጣሉት ታሪፍ የተነሳ የአይፎን ስልክ ዋጋ በሶስት እጥፍ ሊጨምር እንደሚችል ስጋቶች የነበሩ ቢሆንም አሁን ላይ የኤሌክትሮኒክስ ምርቶቹ ከአፀፋዊ ታሪፉ ነፃ መሆን ትልቅ ዕድል እንደሚሆን ተዘግቧል።
በውሳኔው መሰረትም #ሳምሰንግን ጨምሮ ሌሎች አለም አቀፍ የኤሌክትሮኒክስ አምራቾች ወደ አሜሪካ ምርታቸውን ሲልኩ ይጠብቃቸው ከነበረው የ10% መሰረታዊ ታሪፍም ነፃ መሆናቸው ተነግሯል።
ከታሪፉ ነፃ የሆኑ 20 የምርት ዘርፎች የተቀመጡ ሲሆን ለሴሚ ኮንዳክተር መሳሪያነት የሚያገለግሉ ማሽኖችም ከታሪፉ ነፃ መሆናቸው ታውቋል።
ኋይት ሃውስ፣ የአሜሪካ የአለም አቀፍ ንግዶች ኮሚሽን እና የአሜሪካ የንግድ ቢሮ በጉዳዩ ላይ እስካሁን አስተያየት አልሰጡም።
#ዓለምአቀፍ #የታሪፍጦርነት #ቻይና #አሜሪካ
@tikvahethiopia
❤304🤔76🙏24👏21💔16🕊14😭13🥰10😡10😢4😱2
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA #CHINA ቻይና አንዳንድ የአሜሪካ ምርቶችን ከጣለችው የ125% ታክስ ነፃ አደረገች። ቻይና ከአሜሪካ ወደ ሃገሯ የሚገቡ አንዳንድ ምርቶች ከጣለችው የ125% ታሪፍ ነፃ ማድረጓ እና ድርጅቶች ከታክስ ነፃ መሆን አለባቸው ብለው የሚያስቧቸውን ወሳኝ ዕቃዎች ለይተው እንዲለዩ መጠየቋን ሮይተርስ ከምንጮች አረጋግጦ ዘግቧል። የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ለታይም መፅሄት በሰጡት ቃለ መጠይቅ…
#ቻይና #አሜሪካ #ታሪፍ
አሜሪካ እና ቻይና በምርቶቻቸው ላይ ጥለውት የነበረውን ታሪፍ ለመቀነስ ተስማሙ።
ሁለቱ የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤቶች በተደጋጋሚ የአፀፋ ታሪፎችን እርስ በራሳቸው ሲጣጣሉ የነበረ ሲሆን በጄኔቫ ከተደረገ ውይይት በኋላ የአፀፋ ታሪፎቹን በ115% ለመቀነስ ተስማምተዋል።
አሜሪካ በቻይና ምርቶች ላይ ጥላ የነበረውን የ145% ታሪፍ በመቀነስ ወደ 30% ያወረደች ሲሆን ቻይና በአሜሪካ ምርቶች ላይ ጥላ የነበረውን የ125% ታሪፍ ወደ 10% ቀንሳለች።
አዲሱ የታሪፍ ቅነሳም ለሚቀጥሉት 90 ቀናት በስራ ላይ ይቆያል ተብሏል።
የአሜሪካ የግምጃ ቤት ሃላፊው ስኮት ቤሰንት የታሪፍ አፀፋዎቹ ሁለቱም ሃገራት የማይፈልጉት ነው በማለት ሃገራቱ አብረው መነገድ እንደሚፈልጉ ገልፀዋል።
ቤሰንት አዲሱ ስምምነት አንዳንድ ሴክተሮች ላይ የተጣሉ ታሪፎችን እንደማይመለከት የገለፁ ሲሆን አሜሪካ በመድሃኒት፣ ሴሚ ኮንዳክተር እና ብረት ላይ አሁንም ስትራቴጂካዊ የንግድ ሚዛንን ማስጠበቋን ትቀጥላለች ብለዋል።
በተጨማሪ ቻይና ከታሪፍ በተጨማሪ ውድ ማዕድናት ወደ አሜሪካ እንዳይላኩ ያስቀመጠችውን እገዳ ጨምሮ ሌሎች ከታሪፍ ውጪ የሆኑ የንግድ እገዳዎችን ታነሳለች ተብሏል።
የጄኔቫው ውይይት በሁለቱ ሃገራት ከፍተኛ አመራሮች መካከል ከትራምፕ ወደ ስልጣን መመለስ በኋላ የተደረገ የመጀመሪያ ውይይት ሲሆን በጊዜያዊነት ቢሆንም ሃገራቱ ከገቡበት የንግድ ጦርነት ፋታ እንዲወስዱ አድርጓል።
ሁለቱ ሃገራት ወደ ንግድ ጦርነቱ ከገቡ በኋላ የ600 ቢሊየን ዶላር የንግድ እንቅስቃሴ መቆሙ ከመነገሩ በተጨማሪ የሁለቱንም ሃገራት ኢኮኖሚ በክፉኛ ተጎድቷል።
ቻይናና አሜሪካ ይህ የመጀመሪያው ንግግር መሆኑን ያስታወቁ ሲሆን በንግድ እና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ዙሪያ በቀጣይ በቻይና አሊያም በአሜሪካ ወይም በአማራጭነት በሶስተኛ ሃገር ውይይቶች እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
የመረጃው ምንጮች ሲኤንኤን እና ሮይተርስ ናቸው።
@tikvahethiopia
አሜሪካ እና ቻይና በምርቶቻቸው ላይ ጥለውት የነበረውን ታሪፍ ለመቀነስ ተስማሙ።
ሁለቱ የግዙፍ ኢኮኖሚ ባለቤቶች በተደጋጋሚ የአፀፋ ታሪፎችን እርስ በራሳቸው ሲጣጣሉ የነበረ ሲሆን በጄኔቫ ከተደረገ ውይይት በኋላ የአፀፋ ታሪፎቹን በ115% ለመቀነስ ተስማምተዋል።
አሜሪካ በቻይና ምርቶች ላይ ጥላ የነበረውን የ145% ታሪፍ በመቀነስ ወደ 30% ያወረደች ሲሆን ቻይና በአሜሪካ ምርቶች ላይ ጥላ የነበረውን የ125% ታሪፍ ወደ 10% ቀንሳለች።
አዲሱ የታሪፍ ቅነሳም ለሚቀጥሉት 90 ቀናት በስራ ላይ ይቆያል ተብሏል።
የአሜሪካ የግምጃ ቤት ሃላፊው ስኮት ቤሰንት የታሪፍ አፀፋዎቹ ሁለቱም ሃገራት የማይፈልጉት ነው በማለት ሃገራቱ አብረው መነገድ እንደሚፈልጉ ገልፀዋል።
ቤሰንት አዲሱ ስምምነት አንዳንድ ሴክተሮች ላይ የተጣሉ ታሪፎችን እንደማይመለከት የገለፁ ሲሆን አሜሪካ በመድሃኒት፣ ሴሚ ኮንዳክተር እና ብረት ላይ አሁንም ስትራቴጂካዊ የንግድ ሚዛንን ማስጠበቋን ትቀጥላለች ብለዋል።
በተጨማሪ ቻይና ከታሪፍ በተጨማሪ ውድ ማዕድናት ወደ አሜሪካ እንዳይላኩ ያስቀመጠችውን እገዳ ጨምሮ ሌሎች ከታሪፍ ውጪ የሆኑ የንግድ እገዳዎችን ታነሳለች ተብሏል።
የጄኔቫው ውይይት በሁለቱ ሃገራት ከፍተኛ አመራሮች መካከል ከትራምፕ ወደ ስልጣን መመለስ በኋላ የተደረገ የመጀመሪያ ውይይት ሲሆን በጊዜያዊነት ቢሆንም ሃገራቱ ከገቡበት የንግድ ጦርነት ፋታ እንዲወስዱ አድርጓል።
ሁለቱ ሃገራት ወደ ንግድ ጦርነቱ ከገቡ በኋላ የ600 ቢሊየን ዶላር የንግድ እንቅስቃሴ መቆሙ ከመነገሩ በተጨማሪ የሁለቱንም ሃገራት ኢኮኖሚ በክፉኛ ተጎድቷል።
ቻይናና አሜሪካ ይህ የመጀመሪያው ንግግር መሆኑን ያስታወቁ ሲሆን በንግድ እና ኢኮኖሚ ጉዳዮች ዙሪያ በቀጣይ በቻይና አሊያም በአሜሪካ ወይም በአማራጭነት በሶስተኛ ሃገር ውይይቶች እንደሚቀጥሉ ተናግረዋል።
የመረጃው ምንጮች ሲኤንኤን እና ሮይተርስ ናቸው።
@tikvahethiopia
👏479❤106🤔42🕊37🥰26🙏12😡10😭9😢4💔4😱1