TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሶማሊያ መንግሥት ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነት #ለማቋረጥ በመወሰን በአገሪቱ የሚገኙ የኢትዮጵያ አምባሳደር እና ዲፕሎማቶች ለቀው እንዲወጡ ማዘዟ ተሰምቷል። አዲስ አበባ ያሉትን አምባሳደሯንም ጠርታለች። የሶማሊያ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ያሳለፈውን ውሳኔ ተከትሎ የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሚኒስቴር ይፋ እዳደረገው በሶማሊያ የኢትዮጵያ አምባሳደር ሙክታር…
#Update
" የቀን ህልም ነው ... ምንም የማይረባ ፤ እኛን አያሳስበንም " - ሶማሌላንድ
" የሶማሊያ መንግሥት አንዳች ስልጣን የለውም " - ፑንትላንድ
#ፑንትላንድ እና #ሶማሌላንድ የሶማሊያ ፌዴራል መንግሥትን ማስጠንቀቂያ ውድቅ አደረጉ።
የሶማሊያ መንግሥት ፤ #ኢትዮጵያ ከሶማሌላድ ጋር ያደረገችውን የመግባቢያ ስምምነት ምክንያት በማድረግና " በውስጥ ጉዳዬ ጣልቃ እየገባሽ ነው " በማለት ሞቃዲሹ ያሉት የኢትዮጵያ አምባሳደር በ72 ሰዓታት ውስጥ ከሀገሪቱ ለቀው እንዲወጡ አዟል።
ከዚህ ባለፈ ግን በሶማሌላድ ፣ #ሀርጌሳ እና በፑንትላንድ፣ #ጋሮዌ የሚገኙት የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅ/ቤቶች በ7 ቀን እንዲዘጉ አስጠንቅቋል። ኢትዮጵያ ዲፕሎማቶችም በ1 ሳምንት ውስጥ ሀገር ለቀው እንዲወጡ አዟል። ካልሆነ ወደሌላ እርምጃ ገባለሁ ብሏል።
ለዚህ ማስጠንቀቂያ ፑንትላንድ እና ሶማሌላንድ ምላሽ ሰጥተዋል። የሶማሊያ ፌዴራል መንግስትን ማስጠንቀቂያም ውድቅ አድርገዋል።
ዛሬ ምሽት ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ሶማሊኛ ክፍል አጭር ቃላቸውን የሰጡት የሶማሌላንድ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚንስትር አምባሳደር ሮዳ ጃማ ፥ " የቀን ህልም ነው፤ ...ምንም የማይረባ ፤ እኛን አያሳስበንም " ሲሉ ማስጠንቀቂያውን አጣጥለዋል።
የሶማሊያ መንግሥት ስልጣኑ በቪላ ሱማሊያ እና በሙቃዲሾ ዘሌን ቤዝ የተወሰነ መሆኑን በመግለጽ " በውስጥ ጉዳዩ ላይ ቢያተኩር ነው የሚሻለው ... ከአቅሙ በላይ በሆነ ጉዳይ ጊዜ ማባከኑን ማቆም አለበት " ብለዋል።
የፑንትላንድ የማስታወቂያ ሚኒስትር ማህሙድ አይዲድ ድሪር በበኩላቸው " የሶማሊያ ፌደራል መንግስት በጋሮዌ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት የመዝጋት አንዳችም ስልጣን የለውም " ብለዋል።
@tikvahethiopia
" የቀን ህልም ነው ... ምንም የማይረባ ፤ እኛን አያሳስበንም " - ሶማሌላንድ
" የሶማሊያ መንግሥት አንዳች ስልጣን የለውም " - ፑንትላንድ
#ፑንትላንድ እና #ሶማሌላንድ የሶማሊያ ፌዴራል መንግሥትን ማስጠንቀቂያ ውድቅ አደረጉ።
የሶማሊያ መንግሥት ፤ #ኢትዮጵያ ከሶማሌላድ ጋር ያደረገችውን የመግባቢያ ስምምነት ምክንያት በማድረግና " በውስጥ ጉዳዬ ጣልቃ እየገባሽ ነው " በማለት ሞቃዲሹ ያሉት የኢትዮጵያ አምባሳደር በ72 ሰዓታት ውስጥ ከሀገሪቱ ለቀው እንዲወጡ አዟል።
ከዚህ ባለፈ ግን በሶማሌላድ ፣ #ሀርጌሳ እና በፑንትላንድ፣ #ጋሮዌ የሚገኙት የኢትዮጵያ ቆንስላ ፅ/ቤቶች በ7 ቀን እንዲዘጉ አስጠንቅቋል። ኢትዮጵያ ዲፕሎማቶችም በ1 ሳምንት ውስጥ ሀገር ለቀው እንዲወጡ አዟል። ካልሆነ ወደሌላ እርምጃ ገባለሁ ብሏል።
ለዚህ ማስጠንቀቂያ ፑንትላንድ እና ሶማሌላንድ ምላሽ ሰጥተዋል። የሶማሊያ ፌዴራል መንግስትን ማስጠንቀቂያም ውድቅ አድርገዋል።
ዛሬ ምሽት ለቪኦኤ ሬድዮ ጣቢያ ሶማሊኛ ክፍል አጭር ቃላቸውን የሰጡት የሶማሌላንድ የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚንስትር አምባሳደር ሮዳ ጃማ ፥ " የቀን ህልም ነው፤ ...ምንም የማይረባ ፤ እኛን አያሳስበንም " ሲሉ ማስጠንቀቂያውን አጣጥለዋል።
የሶማሊያ መንግሥት ስልጣኑ በቪላ ሱማሊያ እና በሙቃዲሾ ዘሌን ቤዝ የተወሰነ መሆኑን በመግለጽ " በውስጥ ጉዳዩ ላይ ቢያተኩር ነው የሚሻለው ... ከአቅሙ በላይ በሆነ ጉዳይ ጊዜ ማባከኑን ማቆም አለበት " ብለዋል።
የፑንትላንድ የማስታወቂያ ሚኒስትር ማህሙድ አይዲድ ድሪር በበኩላቸው " የሶማሊያ ፌደራል መንግስት በጋሮዌ የሚገኘውን የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽህፈት ቤት የመዝጋት አንዳችም ስልጣን የለውም " ብለዋል።
@tikvahethiopia
❤1.51K🕊167👏125😱82🙏72😡50🤔48😢48😭25🥰20💔1