#ETA
" ማንኛውም የግል ትምህርት ወይም ስልጠና ተቋም #የመምህርነት እና #የህግ ትምህርት ዘርፎችን ማስተማር አይችልም "
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ፤ ባዘጋጀው የከፍተኛ ትምህርትና የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ዘርፍ ፈቃድ አሰጣጥ ረቂቅ መመሪያ ላይ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወይም የስልጠና ተቋማት በሁሉም መርሃ ግብሮች #የሕግ እና #የመምህርነት ትምህርት ዘርፎችን #አሁንም ማስተማር እንደማይችሉ ተገልጿል።
ከዚህ በፊትም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁሉም መርሃግብሮች የሕግ እንዲሁም የመምህርነት ትምህርት እንዳይሰጡ የተደረገ ሲሆን አሁንም በአዲሱ መመሪያ የሕግ እና የመምህርነት ትምህርት መስጠት አይችሉም ተብሏል።
ሌሎች በአዲሱ የከፍተኛ ትምህርትና የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ዘርፍ ፈቃድ አሰጣጥ #ረቂቅ መመሪያ ላይ ምን ተካቷል ?
- ማንኛውም ተቋም አዲስ ፕሮግራም ለመከፈት ወይም ነባሩን ፕሮግራም ለማስቀጠል የፍላጎት ዳሰሳ፣ የገበያ ጥናት እና ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ እውደ ጥናት ማካሄድ ይኖርበታል፡፡
- ለማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት የፕሮግራም ፈቃድ የሚሰጠው ባለስልጣኑ (የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን) የሚያወጣቸውን መስፈርቶች አሟልተው ሲገኙ ብቻ ይሆናል፡፡
- የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚከፍቷቸው ፕሮግራሞች ባለስልጣኑ (የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን) የሚያወጣቸውን የመመዘኛ መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
- ለማንኛውም ተቋም የሚሰጥ ፈቃድ የሚያገለግለው በባለስልጣኑ (የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን) ተገምግሞ ለተፈቀደለት ካምፓስና የትምህርት መስክ ብቻ ይሆናል።
- ማንኛውም ተቋም የጤና የትምህርት መስኮችን መስጠት የሚችለው በመደበኛ መርሃ ግብር ብቻ ይሆናል፡፡
- ማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም በርቀት ትምህርት መርሃ ግብር ማስተማር የሚችለው ከድንበር ተሻጋሪ ወጪ በመጀመሪያ ዲግሪ ብቻ ይሆናል።
- ማንኛውም የግል ትምህርት ወይም ስልጠና ተቋም #የመምህርነት እና #የህግ ትምህርት ዘርፎችን ማስተማር አይችልም፡፡
- ማንኛውም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋም የትኛውንም ስልጠና በርቀት መርሃ ግብር ለማሰልጠን የሚቀርብ የፈቃድ ጥያቄ የማይስተናግድ ይሆናል።
- ማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም #በህክምና_ዶክትሬት እና #በስፔሻሊቲ ትምህርት ፈቃድ ለማግኘት ተቋሙ #የህክምና_ሆስፒታል ሊኖረው ይገባል።
- በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በተቋም ደረጃ የጸደቀ ስርዓተ ትምህርት የፈቃድ ጊዜው ሳያበቃ የስርዓተ ትምህርት ወይም የዲግሪ ስያሜ ለውጥ ካለባለስልጣኑ ፈቃድ ወጪ ማድረግ አይችልም።
- በሀገር ደረጃ በትምህርት ፖሊሲ ስርዓተ ትምህርቱ እስካልተቀየረ ድረስ በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በተቋም ወይም በካምፓስ ደረጃ የጸደቀ ስርዓተ ትምህርት የፈቃድ/ፈቃድ እድሳት ጊዜው እስካላበቃ ድረስ በሌሎች ካምፓሶች መተግበር ወይም መጠቀም ይችላል።
- የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በበየነ መረብ ወይም በርቀት ትምህርት መርሃ-ግብር ፈቃድ ሲጠይቁ በባለስልጣኑ (የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን) ስርዓተ-ትምህርቱ ቀድሞ መገምገም እና ተገቢ ማስተካከያ ተደርጎ መፅደቅ ይኖርበታል።
- ማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም በብሎክ ኮርስ ትምህርት ለመስጠት ያለው አመቺነትና ተገቢነት እንዲሁም የትምህርት ጥራት ላይ የሚኖረውን ተፅህኖ ከግምት በማስገባት ስርዓተ ትምህርቱ ከጸደቀ በኃላ ሊተገብር ይችላል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ያገኘው ከትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን መሪ አስፈፃሚ ሕይወት አሰፋ ነው።
@tikvahethiopia
" ማንኛውም የግል ትምህርት ወይም ስልጠና ተቋም #የመምህርነት እና #የህግ ትምህርት ዘርፎችን ማስተማር አይችልም "
የኢ.ፌ.ዴ.ሪ. ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን ፤ ባዘጋጀው የከፍተኛ ትምህርትና የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ዘርፍ ፈቃድ አሰጣጥ ረቂቅ መመሪያ ላይ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ወይም የስልጠና ተቋማት በሁሉም መርሃ ግብሮች #የሕግ እና #የመምህርነት ትምህርት ዘርፎችን #አሁንም ማስተማር እንደማይችሉ ተገልጿል።
ከዚህ በፊትም የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በሁሉም መርሃግብሮች የሕግ እንዲሁም የመምህርነት ትምህርት እንዳይሰጡ የተደረገ ሲሆን አሁንም በአዲሱ መመሪያ የሕግ እና የመምህርነት ትምህርት መስጠት አይችሉም ተብሏል።
ሌሎች በአዲሱ የከፍተኛ ትምህርትና የቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ዘርፍ ፈቃድ አሰጣጥ #ረቂቅ መመሪያ ላይ ምን ተካቷል ?
- ማንኛውም ተቋም አዲስ ፕሮግራም ለመከፈት ወይም ነባሩን ፕሮግራም ለማስቀጠል የፍላጎት ዳሰሳ፣ የገበያ ጥናት እና ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ እውደ ጥናት ማካሄድ ይኖርበታል፡፡
- ለማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት እና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት የፕሮግራም ፈቃድ የሚሰጠው ባለስልጣኑ (የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን) የሚያወጣቸውን መስፈርቶች አሟልተው ሲገኙ ብቻ ይሆናል፡፡
- የመንግስት ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚከፍቷቸው ፕሮግራሞች ባለስልጣኑ (የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን) የሚያወጣቸውን የመመዘኛ መስፈርቶች ማሟላት ይኖርባቸዋል፡፡
- ለማንኛውም ተቋም የሚሰጥ ፈቃድ የሚያገለግለው በባለስልጣኑ (የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን) ተገምግሞ ለተፈቀደለት ካምፓስና የትምህርት መስክ ብቻ ይሆናል።
- ማንኛውም ተቋም የጤና የትምህርት መስኮችን መስጠት የሚችለው በመደበኛ መርሃ ግብር ብቻ ይሆናል፡፡
- ማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም በርቀት ትምህርት መርሃ ግብር ማስተማር የሚችለው ከድንበር ተሻጋሪ ወጪ በመጀመሪያ ዲግሪ ብቻ ይሆናል።
- ማንኛውም የግል ትምህርት ወይም ስልጠና ተቋም #የመምህርነት እና #የህግ ትምህርት ዘርፎችን ማስተማር አይችልም፡፡
- ማንኛውም የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋም የትኛውንም ስልጠና በርቀት መርሃ ግብር ለማሰልጠን የሚቀርብ የፈቃድ ጥያቄ የማይስተናግድ ይሆናል።
- ማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም #በህክምና_ዶክትሬት እና #በስፔሻሊቲ ትምህርት ፈቃድ ለማግኘት ተቋሙ #የህክምና_ሆስፒታል ሊኖረው ይገባል።
- በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በተቋም ደረጃ የጸደቀ ስርዓተ ትምህርት የፈቃድ ጊዜው ሳያበቃ የስርዓተ ትምህርት ወይም የዲግሪ ስያሜ ለውጥ ካለባለስልጣኑ ፈቃድ ወጪ ማድረግ አይችልም።
- በሀገር ደረጃ በትምህርት ፖሊሲ ስርዓተ ትምህርቱ እስካልተቀየረ ድረስ በከፍተኛ ትምህርት ዘርፍ በተቋም ወይም በካምፓስ ደረጃ የጸደቀ ስርዓተ ትምህርት የፈቃድ/ፈቃድ እድሳት ጊዜው እስካላበቃ ድረስ በሌሎች ካምፓሶች መተግበር ወይም መጠቀም ይችላል።
- የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት በበየነ መረብ ወይም በርቀት ትምህርት መርሃ-ግብር ፈቃድ ሲጠይቁ በባለስልጣኑ (የኢፌዴሪ ትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን) ስርዓተ-ትምህርቱ ቀድሞ መገምገም እና ተገቢ ማስተካከያ ተደርጎ መፅደቅ ይኖርበታል።
- ማንኛውም የከፍተኛ ትምህርት ተቋም በብሎክ ኮርስ ትምህርት ለመስጠት ያለው አመቺነትና ተገቢነት እንዲሁም የትምህርት ጥራት ላይ የሚኖረውን ተፅህኖ ከግምት በማስገባት ስርዓተ ትምህርቱ ከጸደቀ በኃላ ሊተገብር ይችላል፡፡
ቲክቫህ ኢትዮጵያ መረጃውን ያገኘው ከትምህርትና ስልጠና ባለስልጣን መሪ አስፈፃሚ ሕይወት አሰፋ ነው።
@tikvahethiopia
👍1.43K👎239❤175🙏42🥰16🕊14😢12😱8🤔1
🚨#Attention #ቦሌወረዳ11
🔴 “ ወንዙ በአፈር ተዘግቷል። ዶክሜንት፤ ዩኒፎርም፤ ጫማ አልቀረም። ከ100 በላይ አባወራ ሜዳ ላይ ወድቆ ነው ያለው ” - ነዋሪዎች
🔈 “ ምንም እቃ አልቀረልኝም ንብረቴ በስብሶ ነው ያለው። ከነልጆቼ ውጪ ነው ያደረኩት” - እያለቀሱ የተናገሩ አባት
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11፣ ቀጠና 2፣ “ወይናምባ ማርያም” ወደ ኢንዱስትሪ ፓርክ በሚወስደው ትልቁ ወንዝ አካባቢ ያሉ ነዋሪዎች፣ ትላንት በጣለው ዝናብ ከፍተኛ የንብረት ጉዳት እንዳደረሰባቸው፣ ውሃው አሁንም ሙሉ ለሙሉ እንዳልተወገደ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ተናግረዋል።
አንድ እያለቀሱ ሁነቱን ያስረዱ ነዋሪ አባት፦
“ ምንም እቃ አልቀረልኝም። ንብረቴ በስብሶ ነው ያለው። ከነልጆቼ ውጪ ነው ያደረኩት። የተወሰኑ ሰዎች ናቸው የሚሰሩት ነገሩን።
ንብረቱስ ይቅር፤ አሁን ራሱ ቱቦው ተዘጋብን፣ ከነልጆቻችን ከቤት ውጪ ነን። ጭቃው፣ ሽታውና ብዙ ነገሩ በሽተኛ ሆነን ነው ያለነው።
መፍሄው የተዘጋውን ወንዝ መክፈት ነው።
ከ10 ዓመት በላይ የኖርንበት ሰፈር ነው። ከሦስት ዓመት ወዲህ ከበድ ያለ ዝናብ ሲዘንብ ብቻ የተወሰነ የቤት ግድግዳ ነክቶ ነበር የሚያልፈው፣ አሁን ግን ውጪ አሳደረን።
ከወንዙ አፈር የሚደፉ ግለሰቦች አቅምና ብር አላቸው፤ ከወረዳው ጋር ቅኝ እጅ ናቸው። ግለሰቦቹ እያንዳንዳቸው አንድ ክፍለ ከተማ ናቸው። ይታሰሩ አንልም፤ መንግስት አፈሩን ያስነሳልን።
ግለሰቦቹ ወረዳውና ከክፍለ ከተማው አስተዳደር በላይ ናቸው፤ ክፍለ ከተማውም ያውቃል ጉዳዩን ማስፈጸም አልቻለም ላለፉት ሦስት ዓመታት ዘንድሮን ጨምሮ።
አምና ቴሌቪዥን፣ ፍሪጅ ተበላሸብን ገዝተን ተካን፣ ዘንድሮም እንደዚሁ። ሁል ጊዜ ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ ከሚሆንብን ወንዙን የዘጋውን አፈር ያስነሱልን ” ብለዋል።
ሌላኛው ንብረት የተጎዳባቸው ነዋሪ፦
“ እያንዳንዱ ቤት ተማሪዎች አሉ፤ አንድ ዶክሜንት፤ ዩኒፎርም፤ ጫማ አልቀረም።
አፈር በሲኖ እየመጣ ወንዙ ዘግቷል። እዛ ወንዙ ልክ ዝናብ በዘነበ ቁጥር እየሞላ፣ እየሞላ ከሰው ጎርፉ ቤት ገባ።
በአንድ ሰው ብቻ ከ200 ሺሕ በላይ የቤት ቁሳቁስ ነው የወደመው። በአንድ ሰፈር ያለው ከተከራዮች ውጭ ቢያንስ አንድ ግቢ ከ25 እስከ 30 የሚሆን ሰው ነው።
ንብረት አንድም የተረፈን ነገር የለም። አሁንም ሰዎች ወንዝ ዳር፣ ወንዝ ውስጥ ከጭቃ እቃ እየለቀሙ ነው ያሉት።
ከተከራይ ከህፃናት እስከ አዋቂ ሁሉም ፀሐይ ላይ ነው። ከህዳር ወር ጀምሮ ነው አቤቱታ እያቀረብን የነበረነው። ይሄው ከባድ ዝናብ የዘነበው ትላንትና ከቀኑ 9 እስከ 10 ሰዓት አካባቢ ጀምሮ ነው።
ወንዝ መሄጃ መንገዱን በግራና በቀኝ እየደፉ ገቡ የዛሬ አመት እንዲሁ ስንጨናነቅ ድልድዩ ወደቀ፤ ድልድዩን እያንዳንዱ ማህበረሰብ 500 ብር አዋጥቶ አስነሳ።
ዋናው ነገር አሁን ድረሱልን። ህዝብ ከሌለ መንግስት ብቻውን መቀመጥ አይችልም። የሄን ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉት ደግሞ ሦስት ሰዎች ናቸው። ስለነዚህ ሰዎች ወረዳውን ስንጠይቀው ምንም የሚሰጠው ምላሽ የለም።
‘እናስተካክላለን፣ ለክፍለ ከተማ አመልክተናል’ ነው የሚሉት ሌላ የተሰጠ አማራጭ የለም። በምትችሉት ለነፍሳችን ድረሱልን” ነው ያሉት።
ሌላኛው የስፍራው ነዋሪ ፦
“ በጣም ችግር አለ። ተደጋጋሚ ነው። የዛሬ ሁለት፤ ሦስት ዓመታት ሆኖታል። ይሄ ሁሉ የሚሆነው በሦስት፤ አራት አባወራ ግለሰቦች ነው።
አፈር እየደፉ ወንዙን የዘጉት። ከሳይት የሚመጣ አፈር እያስደፉ፣ ብር ይቀበላሉ፤ ወንዙን ዘጉት ውሃው በየት ይሂድ። እስከ ወረዳና ክፍለ ከተማ ድረስ ይታወቃሉ፤ ግን ምንም መፍትሄ ነገር አልተሰጠም።
የተከራዮቸ፣ የኔ ሙሉ የቤት እቃ፣ ደብተርና ዩኒፎርም ሙሉው የለም። አሁንም ቢዘንብ ተመልሶ ይገባል።
#አሁንም ጎርፉ እንዳለ ነው። ለሚመለከተው ተናግረን ነው የመጣነው አሁን፤ ‘ክሰሱ’ ነው የተባልነው። እኛ ደግሞ አሁን አንገብጋቢ ቾግር ነው ያለብን። ዝናብ ቢጥል ተመልሶ ከቤት ነው የሚገባው።
ወረዳው፤ ክፍለ ከተማው ምንም መፍትሄ አልሰጡንም። ‘እናስጠርጋለን ነው’ የሚሉት። ከ100 በላይ አባወራ ሜዳ ላይ ወድቆ ነው ያለው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለእሳትና አደጋ ሥራ አመራር ከሸሚሽን ቅሬታውን አሁን አድርሷል። ጉዳዩን ተከታትለን መረጃ እናቀርባለን።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
🔴 “ ወንዙ በአፈር ተዘግቷል። ዶክሜንት፤ ዩኒፎርም፤ ጫማ አልቀረም። ከ100 በላይ አባወራ ሜዳ ላይ ወድቆ ነው ያለው ” - ነዋሪዎች
በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 11፣ ቀጠና 2፣ “ወይናምባ ማርያም” ወደ ኢንዱስትሪ ፓርክ በሚወስደው ትልቁ ወንዝ አካባቢ ያሉ ነዋሪዎች፣ ትላንት በጣለው ዝናብ ከፍተኛ የንብረት ጉዳት እንዳደረሰባቸው፣ ውሃው አሁንም ሙሉ ለሙሉ እንዳልተወገደ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ዛሬ ተናግረዋል።
አንድ እያለቀሱ ሁነቱን ያስረዱ ነዋሪ አባት፦
“ ምንም እቃ አልቀረልኝም። ንብረቴ በስብሶ ነው ያለው። ከነልጆቼ ውጪ ነው ያደረኩት። የተወሰኑ ሰዎች ናቸው የሚሰሩት ነገሩን።
ንብረቱስ ይቅር፤ አሁን ራሱ ቱቦው ተዘጋብን፣ ከነልጆቻችን ከቤት ውጪ ነን። ጭቃው፣ ሽታውና ብዙ ነገሩ በሽተኛ ሆነን ነው ያለነው።
መፍሄው የተዘጋውን ወንዝ መክፈት ነው።
ከ10 ዓመት በላይ የኖርንበት ሰፈር ነው። ከሦስት ዓመት ወዲህ ከበድ ያለ ዝናብ ሲዘንብ ብቻ የተወሰነ የቤት ግድግዳ ነክቶ ነበር የሚያልፈው፣ አሁን ግን ውጪ አሳደረን።
ከወንዙ አፈር የሚደፉ ግለሰቦች አቅምና ብር አላቸው፤ ከወረዳው ጋር ቅኝ እጅ ናቸው። ግለሰቦቹ እያንዳንዳቸው አንድ ክፍለ ከተማ ናቸው። ይታሰሩ አንልም፤ መንግስት አፈሩን ያስነሳልን።
ግለሰቦቹ ወረዳውና ከክፍለ ከተማው አስተዳደር በላይ ናቸው፤ ክፍለ ከተማውም ያውቃል ጉዳዩን ማስፈጸም አልቻለም ላለፉት ሦስት ዓመታት ዘንድሮን ጨምሮ።
አምና ቴሌቪዥን፣ ፍሪጅ ተበላሸብን ገዝተን ተካን፣ ዘንድሮም እንደዚሁ። ሁል ጊዜ ውሃ ቅዳ ውሃ መልስ ከሚሆንብን ወንዙን የዘጋውን አፈር ያስነሱልን ” ብለዋል።
ሌላኛው ንብረት የተጎዳባቸው ነዋሪ፦
“ እያንዳንዱ ቤት ተማሪዎች አሉ፤ አንድ ዶክሜንት፤ ዩኒፎርም፤ ጫማ አልቀረም።
አፈር በሲኖ እየመጣ ወንዙ ዘግቷል። እዛ ወንዙ ልክ ዝናብ በዘነበ ቁጥር እየሞላ፣ እየሞላ ከሰው ጎርፉ ቤት ገባ።
በአንድ ሰው ብቻ ከ200 ሺሕ በላይ የቤት ቁሳቁስ ነው የወደመው። በአንድ ሰፈር ያለው ከተከራዮች ውጭ ቢያንስ አንድ ግቢ ከ25 እስከ 30 የሚሆን ሰው ነው።
ንብረት አንድም የተረፈን ነገር የለም። አሁንም ሰዎች ወንዝ ዳር፣ ወንዝ ውስጥ ከጭቃ እቃ እየለቀሙ ነው ያሉት።
ከተከራይ ከህፃናት እስከ አዋቂ ሁሉም ፀሐይ ላይ ነው። ከህዳር ወር ጀምሮ ነው አቤቱታ እያቀረብን የነበረነው። ይሄው ከባድ ዝናብ የዘነበው ትላንትና ከቀኑ 9 እስከ 10 ሰዓት አካባቢ ጀምሮ ነው።
ወንዝ መሄጃ መንገዱን በግራና በቀኝ እየደፉ ገቡ የዛሬ አመት እንዲሁ ስንጨናነቅ ድልድዩ ወደቀ፤ ድልድዩን እያንዳንዱ ማህበረሰብ 500 ብር አዋጥቶ አስነሳ።
ዋናው ነገር አሁን ድረሱልን። ህዝብ ከሌለ መንግስት ብቻውን መቀመጥ አይችልም። የሄን ጉዳት እንዲደርስ ያደረጉት ደግሞ ሦስት ሰዎች ናቸው። ስለነዚህ ሰዎች ወረዳውን ስንጠይቀው ምንም የሚሰጠው ምላሽ የለም።
‘እናስተካክላለን፣ ለክፍለ ከተማ አመልክተናል’ ነው የሚሉት ሌላ የተሰጠ አማራጭ የለም። በምትችሉት ለነፍሳችን ድረሱልን” ነው ያሉት።
ሌላኛው የስፍራው ነዋሪ ፦
“ በጣም ችግር አለ። ተደጋጋሚ ነው። የዛሬ ሁለት፤ ሦስት ዓመታት ሆኖታል። ይሄ ሁሉ የሚሆነው በሦስት፤ አራት አባወራ ግለሰቦች ነው።
አፈር እየደፉ ወንዙን የዘጉት። ከሳይት የሚመጣ አፈር እያስደፉ፣ ብር ይቀበላሉ፤ ወንዙን ዘጉት ውሃው በየት ይሂድ። እስከ ወረዳና ክፍለ ከተማ ድረስ ይታወቃሉ፤ ግን ምንም መፍትሄ ነገር አልተሰጠም።
የተከራዮቸ፣ የኔ ሙሉ የቤት እቃ፣ ደብተርና ዩኒፎርም ሙሉው የለም። አሁንም ቢዘንብ ተመልሶ ይገባል።
#አሁንም ጎርፉ እንዳለ ነው። ለሚመለከተው ተናግረን ነው የመጣነው አሁን፤ ‘ክሰሱ’ ነው የተባልነው። እኛ ደግሞ አሁን አንገብጋቢ ቾግር ነው ያለብን። ዝናብ ቢጥል ተመልሶ ከቤት ነው የሚገባው።
ወረዳው፤ ክፍለ ከተማው ምንም መፍትሄ አልሰጡንም። ‘እናስጠርጋለን ነው’ የሚሉት። ከ100 በላይ አባወራ ሜዳ ላይ ወድቆ ነው ያለው።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለእሳትና አደጋ ሥራ አመራር ከሸሚሽን ቅሬታውን አሁን አድርሷል። ጉዳዩን ተከታትለን መረጃ እናቀርባለን።
#TikvahEthiopiaFamilyAA
@tikvahethiopia
Please open Telegram to view this post
VIEW IN TELEGRAM
😭871❤161😢114🙏50🕊23🤔16🥰10😱9👏6💔3😡3