TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63K photos
1.61K videos
216 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#ኢትዮጵያ ሀገራችን ኢትዮጵያ በቡዳፔስት የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮና የመጨረሻዋ ውድድር የሆነውን የሴቶች 3000ሜ መሰናክል ውድድር ማድረግ ጀምራለች። በውድድሩ ሀገራችን ፦ - በአትሌት ሲምቦ አለማየሁ - በአትሌት ዘርፌ ወንድማገኝ - በአትሌት ሎሜ ሙለታ ተወክላለች። መልካም ዕድል ! @tikvahethiopia
#ተጠናቋል

በዚህም ድል አልቀናንም !

በሴቶች 3000 ሜትር መሰናክል ኢትዮጵያ ድል አልቀናትም።

ዘርፌ ወንድማገኝ 4ኛ ደረጃ ይዛ አጠናቃለች።

ሎሜ ሙለታ 12ኛ ፣ ሲምቦ አለማየሁ 13ኛ ደረጃ ይዘው አጠናቀዋል።

ሀገራችን በሀንጋሪ፣ ቡዳፔስት ስታካሂድ የነበረውን ውድድሮች ሁሉ #አጠናቃለች

ኢትዮጵያ በሜዳሊያ ብዛት ከዓለም 6ኛ ደረጃ፣ ከአፍሪካ ደግሞ ኬንያን በመከተል 2ኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች። ኢትዮጵያ 2 የወርቅ፣ 4 የብር እና 3 የነሐስ በድምሩ 9 ሜዳሊያዎችን ነው ያገኘችው።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ዋና ገፅ / @tikvahethiopia ስፖርት በተለይ አትሌቲክስ #ሀገራዊ ስሜትን ፣ አብሮነትን ፣ አንድነትን ያጠነክራል የሚል እምነት ስላለው የሀገራችን ልጆች የተካፈሉባቸውን ውድድሮች ሁሉ #ከስፍራው ከፎቶ ጋር ሲያደርስ ቆይቷል።

ስፖርታዊ መረጃዎችን በ @tikvahethsport መከታተል ትችላላችሁ።

#TikvahFamily

@tikvahethiopia
👎1.17K👍955😢368234👏77🙏45🕊33🥰32😱29
TIKVAH-ETHIOPIA
#AU #ETHIOPIA ትላንትና ምሽት ላይ ለ37ኛው የአፍሪካ ኅብረት የመሪዎች ጉባዔ ለመጡ መሪዎች በብሄራዊ ቤተመንግስት የእራት ግብዣ ተደርጎላቸው ነበር። ዛሬ የጠ/ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ባሰራጫቸው ምስሎች የኬንያው ፕሬዜዳንት ዊሊያም ሩቶ ፣ የጅቡቲ ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌህን ጨምሮ የሌሎች የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች በእራት ግብዣው ላይ ተገኝተው የነበረ ሲሆን የጎረቤት ሶማሊያው ፕሬዜዳንት ሀሰን…
#Update #ተጠናቋል

የአፍሪካ ሕብረት ጉባኤ በሰላምና በስኬት #መጠናቀቁን ኢትዮጵያ አስታውቃለች።

የሁሉም ሀገራት መሪዎች እና የጉባኤው ተሳታፊዎች ወደ አዲስ አበባ ሲገቡ ከዚህ ቀደም ከነበረው በደመቀ ሁኔታ ዓለም አቀፍ የዲፕሎማሲ ክብርን እና ፕሮቶኮልን በጠበቀ መልኩ አቀባበል እንደተደረገላቸው ፤ በአዲስ አበባ ቆይታቸውም በልዩ እንክብካቤ እንደተያዙ በኢትዮጵያ መንግሥት ተገልጿል።

ኢትዮጵያ ለዚህ ጉባኤ ስኬት ላለፉት 6 ወራት ስትዘጋጅ መቆየቷን የተገለጸ ሲሆን በተለይም ከሰላምና ደህንነት አንፃር በርካታ ባለድርሻ አካላት ሲሳተፉ መቆየታቸውን ተጠቁሟል።

በ10 ሺዎች የሚቆጠሩ የፀጥታ እና ደህንነት ኃይሎች ተሰማርተው እንደነበረም ተመላክቷል።

ለጉባኤው ስኬታማነት በተለይ በተለይ የአዲስ አበባ ህዝብ ከቅድመ ጉባኤው ዝግጅት አንስቶ ስብሰባው ተጀምሮ እስኪያልቅ ድረስ የትራፊክ፣ የመንገድ መዘጋጋት እና ሌሎች ጉዳዮችንም ታግሶ ፤ ከፀጥታ ኃይሉም ጋር በመተባበር እንግዶች ደህንነታቸው ተጠብቆ እንዲስተናገዱ ልዩ የእግዳ አቀባበል በማድረጉ መንግሥት ምስጋና አቅርቧል።

በተጨማሪ የፀጥታ እና ደህንነት ኃይሎች ፣ የትራፊክ ተቆጣጣሪዎች፣ የፕሮቶኮል ሰዎች፣ ሆቴሎች ፣ የሀገር ውስጥ እና የውጭ መገናኛ ብዙሃን .. ሌሎችም አስተዋፅኦ ያደረጉ ሁሉ ምስጋና ቀርቦላቸዋል።

@tikvahethiopia
👏729137😡100🕊44🙏24😢17😭11😱7🥰6
TIKVAH-ETHIOPIA
🚨BREAKING🚨 ኢራን እስራኤል ላይ የድሮን ጥቃት ከፈተች። ከዛሬ 12 ቀናት በፊት እስራኤል በሶሪያ የኢራን ቆንስላ ጽ/ቤት ላይ እንደፈፀመችው በተነገረ የአየር ጥቃት ከፍተኛ የኢራን ጄኔራልን ጨምሮ 13 ሰዎች ተገድለዋል። እስራኤል ለግድያው ኃላፊነቱን ባትወስድም ኢራን እሷ እንደሆነች ነው የምታምነው። ይህን ተከትሎ ኢራን የበቀል እርምጃ እንደምትወስድ ስትዝት ቆይታለች። መዛት ብቻ ሳይሆን ዝግጅትም…
#UPDATE

ኢራን ለሊቱን እስራኤልን በድሮን ፣ በሚሳኤልና ሮኬቶች ስትደበድብ ከቆየች በኃላ " እስራኤልን የመቅጣቱ ተግባር #ተጠናቋል " ብላለች።

እስራኤል ማንኛውም አፀፋዊ ምላሽ ሰጣለሁ ካለች ግን ከአሁኑ እጅግ በጣም የከፋው ቅጣት ይጠብቃታል ሲትል አስጠንቅቃለች።

ኢራን የትኛውም ህዝባዊ ይሁን ኢኮኖሚያዊ ዒላማዋች እንዳልነበሯት ዒላማዋ የእስራኤል ወታደራዊ ስፍራዎችና አቅም ላይ እንደነበር ገልጻለች።

ኢራን ለመጀመሪያ ጊዜ ነው በእስራኤል ላይ እንዲህ ያለውም ቀጥተኛ መጠነ ሰፊ ጥቃት የከፈተችው።

ከ360 በላይ ሚሳኤል እና ድሮኖች ከኢራን፣ ኢራቅ፣ የመን ወደ እስራኤል መወንጨፋቸውን የእስራኤል ሠራዊት አስታውቋል።

አብዛኞቹ ጉዳት ሳያደርሱ (99%) በእስራኤል እና በወዳጆቿ አማካይነት እንዲከሽፉ መደረጋቸው ተገልጿል።

ያም ሆኑ በጥቃቱ መጠነኛ ጉዳት መድረሱ ተነግሯል።

እስራኤል የለሊቱን ጥቃት ብቻ ለመመከት 1 ቢሊዮን ዶላር ሳታወጣ አልቀረችም ተብሏል።

የአሜሪካ ጦር በርካታ ሚሳኤሎችን እና ድሮኖችን ከአየር ላይ እንዲከሽፉ አድርጓል። ፕሬዜዳንቷም " እስራኤል የኢራንን ጥቃት የመከተችው በአሜሪካ ድጋፍ ነው " ብለዋል።

ዩናይትድ ኪንግደም እና ፈረንሳይም ከጥቃቱ በፊት የአየር ቅኝት በማድረግ እስራኤልን ሲያግዙ አንግተዋል።

ጆርዳን በአየር ክልሏ ሲያልፉ የነበሩ ድሮኖችን እየመታች የጣለች ሲሆን ይህንን " ለህዝቤ ደህንነት ስል ያደረኩት ነው " ብላለች።

ኢራንም ጆርዳንን " አርፈሽ ካልተቀመጥሽ አንቺም ልክ እንደ እስራኤል ትመቻለሽ " ስትል ዝታባታለች።

እስራኤል በቀጣይ የአፀፋ እርምጃ ትወስድ ይሆን ? የሚለው ብዙዎችን ያሳሰበ ጉዳይ ሲሆን " አሜሪካ ተያት አፀፋ አትውሰጂ " ብላታለች።

ቀድሞኑ በእራኤል እና ፍልስጤም ሀማስ  ጦርነት የተለያየ አቋም ያላቸው የተለያዩ ሀገራትና ተቋማት በጉዳዩ ላይ ያላቸውን ስጋት ገልጸዋል። ውጥረቱ ይረግብ ዘንድ ጥሪ አቅርበዋል።

ኢራን ፥ እስራኤልን የደበደበችው ከዛሬ 13 ቀን በፊት በሶሪያ የኢራን ቆንስላ ጽ/ቤት ላይ እስራኤል እንደፈፀመችው በምታምነው የአየር ጥቃት ከፍተኛ ጄኔራሏን ጨምሮ አጠቃላይ 13 ሰዎች በመገደላቸው ለሱ አፀፋ ነው።

መረጃው ከዓለም አቀፍ የዜና አውታሮች የተሰባሰበ ነው።

More⬇️
https://tttttt.me/+LM-bJ8NzZMcxMjA8

@tikvahethiopia
1.57K👏428🕊221😡196😭125😱63🙏61🤔45😢40🥰23