TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update " በሁለት ሶስት ቀን ውስጥ ሽረ ላይ ስብሰባ ይደረጋል ፤ በአንዳንድ ቴክኒካል ጉዳዮች ዘሪያ የሁለቱም ጦር ተወካዮች ተገናኝተው ይወያያሉ " ትላንት በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል የተካሄደውን የሰላም ድርድር / ስምምነቱን የመሩት የቀድሞው የናይጄሪያው ፕሬዜዳንት የአሁኑ የአፍሪካ ህብረት የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛ ኦሊሴንጉን ኦባሳንጆ የትግራይ መዲና ፤ #መቐለ መግባታቸው…
#Update #ሽረ

የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚኒኬሽን ፤ የትግራይ ታጣቂዎች ትጥቅ የሚፈቱበትን ዝርዝር ዕቅድ የሚሠራው የባለሞያዎች የጋራ ኮሚቴ ሽረ ላይ እየመከረ መሆኑን አሳውቋል።

" በፕሪቶሪያው የሰላም ስምምነት መሠረት ሕወሓት ትጥቅ የሚፈታበትን ዝርዝር ዕቅድ የሚያዘጋጀው የባለሞያዎች የጋራ ኮሚቴ ከትናንት ሕዳር 21 ቀን ጀምሮ ሽረ ላይ ሥራውን ጀምሯል " ያለው የኮሚኒኬሽን አገልግሎት ፤ " ከፌዴራል መንግሥትና ከትግራይ ታጣቂዎች የተውጣጣው የባለሞያዎች የጋራ ኮሚቴ በቀጣይ ጥቂት ቀናት ሥራውን ያጠናቅቃል ተብሎ ይታመናል " ብሏል።

ኮሚቴው የሚያወጣው ዝርዝር ዕቅድ ትጥቅ የማስፈታት፣ ካምፕ የማስገባትና ተያያዥ ጉዳዮችን የሚመልስ እንደሚሆንም ተመላክቷል።

የኢፌዴሪ መንግስት ኮሚኒኬሽ ፤ ዝርዝር ዕቅዱን የማውጣት ተግባሩ፣ በቴክኒክ ጉዳዮች ምክንያት መዘግየቱን ገልጿል።

ፎቶ ፦ ፋይል

@tikvahethiopia
👍543🕊72👎5922🙏13
#ሽረ

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከሰኞ ታህሳስ 24 ቀን 2015 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሽረ ከተማ በቀን አንድ በረራ ማድረግ እንደሚጀምር ዛሬ ገልጿል።

አየር መንገዱ ፤ ወደ መቐለ የሚያደርገውን መደበኛ በረራ በቀን ወደ ሶስት ከፍ የሚያደርግ መሆኑንም አሳውቋል።

በተከታታይም የመንገደኛ ፍላጎት ቁጥርን ከግምት ውስጥ በማስገባት በቀን የሚያደርገውን የበረራ ምልልስ ብዛት እንደሚጨምርም ገልጿል።

አየር መንገዱ ደንበኞቹ ባሉበት ቦታ ሆነው ባድረ ገፀ እና የተንቀሳቃሽ ስልክ መተግበሪያ ተጠቅመው ምዝገባ ማድረግና ትኬት መቁረጥ ይችላሉ ተብሏል።

www.ethiopianairlines.com
bit.ly/ET-android-app
bit.ly/ET-iOS-App

#የኢትዮጵያአየርመንገድ

@tikvahethiopia
👍801🕊18072🙏50😱26😢13🥰11👎1
#ሽረ

" የነቀዘ ፣ የተበላሸና መጥፎ ጠረን ያለው የአርዳታ ዱቄት እየተሰጠን ነው " - ተፈናቃዮች

" ጉዳዩን ደርሼበት የታደለው የተበላሸ ዱቄት እንዲሰበሰብ የሚያስጠነቅቅ ደብዳቤ ፅፊያለሁ "  - የእንዳስላሰ ሽረ ከተማ አስተዳደር

በትግራይ ክልል፣ ሰሜን ምዕራብ ዞን እንዳስላሰ ሽረ ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች ለድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን በሰጡት ቃል ፤ የተበላሸ ፣መጥፎ ጠረን ያለው እና የነቀዘ ዱቄት ከለጋሽ ደርጅቶች መታደላቸውን ገልጸዋል።

ላለፉት 13 ወራት የረባ ሰብአዊ እርዳታ ባለማግኘታቸው በከባድ ችግር ውስጥ እንደሚገኙ የገለፁት ተፈናቃዮቹ ፤ ከረጅም ጊዚያት በኃላ ጥር 20/2016 ዓ.ም መሰጠት የተጀመረው ዱቄት ጥራት የሌለው ፣ የተበላሽ ፣ የነቀዘና መጥፎ ጥረን ያለው መሆኑ በማስረጃ አስደግፈው አቅርበዋል። 

የቴሌቪዥን ጣቢያው " ለተፈናቃዮቹ የተሰጠው ዱቄት ለምግብነት ቢያውሉት ለጤናቸው ጠንቅ እንደሚሆን የምግብ ባለሙያዎች አረጋግጠውልኛል " ብሏል።  

ዱቄቱ በእርዳታ ያከፋፈሉ ለጋሽ ድርጅቶች 'ተበላሸ' ስለተባለው እህል ምላሽ እንዲሰጡ የተደረገው ተደጋጋሚ ሙከራ አልተሳካም።

ጉዳዩ በጥብቅ እየተከታተለው መሆኑ የገለፀው የእንዳስላሰ ሽረ መንግስታዊ አገልግሎት ፅህፈት ቤት ፤  ዱቄቱ ያከፋፈሉ ለጋሽ ድርጅቶች ያደሉት እንዲሰበስቡና ማደል እንዲያቆሙ የሚጠይቅ ደብዳቤ መፃፉን አስታውቋል።

ፅህፈት ቤቱ ለለጋሽ ድርጅቶች በፃፈው ደብዳቤ በመጋዝን የተከማቸውና ለተፈናቃዮች የታደለው ዱቄት ተዘዋውሮ መመልከቱንና የተበላሸ መሆኑ ማረጋገጡ ገልጿል።

ስለሆነም ዱቄቱ በላፕራቶሪ ተጨማሪ ምርመራ እስኪደረግለት ድረስ Lot No. 1 MFD March 2023 & Exp. /Best Before February 2024 በሚል የሚታወቅ የተከማቸና ወደ ተፈናቃዮች የደረሰ ዱቄት እንዲሰበሰብና እንዲከለከል በፃፈው ደብዳቤ ማስጠንቀቁን የድምፂ ወያነ ቴሌቪዥን ዋቢ በማድረግ የመቐለው የቲክቫህ ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባል መረጀውን አጋርቷል።
                  
@tikvahethiopia            
😢712😭275😡106104🕊18🥰13🙏9😱8👏3