TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.8K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
#USA #ETHIOPIA " አሜሪካ ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር ትቆማለች ፤ የአፍሪካ ህብረትን (AU) ዲፕሎማሲያዊ ጥረትን ትደግፋለች " - አንቶኒ ብሊንከን የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ሀገራቸው አሜሪካ #ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር እንደምትቆም እና በአፍሪካ ህብረት እየተመራ ያለውን ዲፕሎማሲያዊ ጥረት #እንደምትደግፍ ገልፀዋል። ይህን የገለፁት ለሊት ባወጡት መግለጫ ነው። ብሊንከን ፤…
#USA #ETHIOPIA

" ለኢትዮጵያ አንድነት ፣ ሉዓላዊነት እና የግዛት አንድነት ቁርጠኛ ነን " - አሜሪካ

አሜሪካ የአፍሪካ ቀንድ ልዩ መልዕክተኛዋ አምባሳደር ማይክ ሀመር ኢትዮጵያን በጎበኙበት ወቅት ከኢትዮጵያ መንግስት ባለስልጣናት ፣ ከሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች፣ ከአፍሪካ ህብረት እና ከዓለም አቀፍ አጋሮች ጋር #ውጤታማ ውይይት አድርገዋል ስትል አሳወቀች።

ሀገሪቱ ይህን ያሳወቀችው ዛሬ አዲስ አበባ በሚገኘው ኤምባሲው በኩል ነው።

የአምባሳደር ማይክ ሐመር የኢትዮጵያ ጉብኝት ውጤታ ነበር ያለችው አሜሪካ  " ለኢትዮጵያ #አንድነት#ሉዓላዊነት እና #የግዛት_አንድነት ቁርጠኛ ነን " ስትል አስታውቃለች።

በተጨማሪ ሁሉም ኢትዮጵያውያን እንዲበለጽጉ ሰላምና መረጋጋትን ለማስፈን የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ እንደምትፈልግ ገልፃለች።

@tikvahethiopia
👎792👍516🙏2221😱20😢13🥰12🕊1
TIKVAH-ETHIOPIA
#Update የሰላም ስምምነቱን አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና አቶ ጌታቸው ረዳ ተፈራርመዋል። ከተፈራረሙ በኃላም እጅ ለእጅ ተጨባብጠዋል። በአጠቃላይ የተደረሱትን የስምምነት ነጥቦችን የያዘው እና በኢትዮጵያ መንግስት እና በህወሓት መካከል (አምባሳደር ሬድዋን ሁሴን እና አቶ ጌታቸው ረዳ) የተፈረመበት ወረቀት እንደደረሰን የምንልክላችሁ ይሆናል። @tikvahethiopia
#Update

ዛሬ በፕሪቶሪያ ፤ በኢትጵያ መንግስት እና ህወሓት መካከል የተፈረመው የሰላም ስምምነትን በተመለከተ የወጣው የጋራ መግለጫ 12 ነጥብ የያዘ ነው።

ከዚህም ስምምነት መካከል ፦

- የህወሓት ቡድን #ትጥቅ_እንዲፈታ ከስምምነት ተደርሷል።

- የኢትዮጵያን #ሉዓላዊነት እና #የግዛት_አንድነት ለማረጋገጥ እና የኢፌደሪ ሕገ-መንግሥቱን ለማስከበር የኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት ተስማምተዋል።

- ኢትዮጵያ #አንድ ብሔራዊ መከላከያ ኃይል ብቻ አላት በሚለው ስምምነት ተፈርሟል።

- በመሬት ላይ ያለውን የፀጥታ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት የህወሓት ተዋጊዎችን ትጥቅ ለማስፈታት፣ ተዋጊዎችን ከሠራዊቱ እንዲወጡ ለማድረግ እና መልሶ ወደ ማኅበረሰቡ ለመቀላቀል ስምምንት ላይ ተደርሷል።

- #የጥይት_ድምጽ_በዘላቂነት_እንዳይሰማ  በመስማማት፣ ጦርነቱ እንዲያበቃ የሚያስችል ዘላቂ የግጭት ማስወገድ ስምምነት ተፈርሟል።

-  በትግራይ ክልል ህገ መንግስታዊ ስርዓትን ወደነበረበት ለመመለስ እና የሽግግር እርምጃዎችን ተግባራዊ ለማድረግ ስምምነት ተፈርሟል።

- የጥላቻ ፕሮፓጋንዳ ለማቆም ስምምነት ላይ ተደርሷል።

- በትግራይ ክልል መሰረታዊ አገልግሎት ወደ ነበረበት እንዲመለስ ስምምነት ተፈፅሟል።

@tikvahethiopia
👍4.37K🕊2.04K👎430408🙏280😢83😱72😭1
" በደቡብ አፍሪካ በነበረው ድርድር ኢትዮጵያ መቶ በመቶ ያቀረበችው ሀሳብ ተቀባይነት አግኝቷል " - ዶ/ር ዐቢይ አህመድ

የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር ዐቢይ አህመድ በስራ ጉብኝት በጋሞ ዞን፣ አርባ ምንጭ ይገኛሉ።

በአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ አባያ ካምፓስ በተካሄደ ስነስርዓት ላይ ለአርባምንጭና ለአካባቢው ህዝብ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በዚህ ወቅት ስለ ደቡብ አፍሪካ ድርድር ስምምነት የተወሰኑ ሀሳቦችን አንስተው ተናግረዋል።

ምን አሉ ?

- የኢትዮጵያ #ሉዓላዊነት እና #የግዛት_አንድነት ለድርድር አይቀርብም በሚለው በሁለቱም ወገን (በመንግስት እና ህወሓት ማለታቸው ነው) ተቀባይነት አግኝቷል።

- በአንድ ሀገር ወስጥ #ከአንድ መከላከያ በላይ አያስፈልግም በሚለውም ጉዳይ ከስምምነት ተደርሷል።

- በትግራይ ክልል ህገወጥ በሆነ መንገድ የተደረገው ምርጫ በህጋዊ ምርጫ መተካት አለበት የሚለውም በሁለቱም ወገኖች (በኢትዮጵያ መንግስት እና ህወሓት) ተቀባይነት አግኝቷል።

- በአንዳንድ ቦታዎች ላይ ያለው የይገባኛል ጥያቄ የሚነሳባቸው እና አከራካሪ ቦታዎች የሰው ልጆችን ህይወት ሳይጠይቁ በሰላም፣ በድርድር እና በሀገሪቱ ህግ መሰረት ብቻ ምላሽ እንዲያገኙ በሁለቱም ወገኖች መተማመን ላይ ተደርሷል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ ፤ በደቡብ አፍሪካ በነበረው የሰላም ድርድር ኢትዮጵያ መቶ በመቶ ያቀረበችው ሀሳብ ተቀባይነት ማግኘቱን ገልፀዋል።

@tikvahethiopia
👍1.61K🕊396👎26482🙏51😱25😢23