TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
" ወ/ሮ ጁዋሪያ መሀመድ ከአንድ የፀጥታ ሀይል አባል በተተኮሰ ጥይት ህይወታቸው አልፏል " - ብልፅግና ፓርቲ
የሶማሌ ክልል ምክር ቤት አባል እና የብልፅግና ፓርቲ ማእከላዊ ኮሚቴ አባል የሆኑት ወ/ሮ ጁዋሪያ መሀመድ ኢብራሂም በ" ጅግጅጋ ኤርፖርት " ውስጥ ከአንድ የፀጥታ ሀይል አባል በተተኮሰ ጥይት ህይወታቸው ማለፉን ብልፅግና ፓርቲ አሳውቋል።
" ጉዳዩ #በህግ_አግባብ ተይዞ እየተጣራ ነው " ያለው ፓርቲው " በቀጣይ ሁኔታው የደረሰበት ደረጃ በሚመለከተው አካል ይገለፃል " ብሏል።
ፓርቲው በማእከላዊ ኮሚቴ አባሉ ላይ በደረሰው ህልፈት ሀዘን እንደተሰማው ገልጿል።
@tikvahethiopia
" ወ/ሮ ጁዋሪያ መሀመድ ከአንድ የፀጥታ ሀይል አባል በተተኮሰ ጥይት ህይወታቸው አልፏል " - ብልፅግና ፓርቲ
የሶማሌ ክልል ምክር ቤት አባል እና የብልፅግና ፓርቲ ማእከላዊ ኮሚቴ አባል የሆኑት ወ/ሮ ጁዋሪያ መሀመድ ኢብራሂም በ" ጅግጅጋ ኤርፖርት " ውስጥ ከአንድ የፀጥታ ሀይል አባል በተተኮሰ ጥይት ህይወታቸው ማለፉን ብልፅግና ፓርቲ አሳውቋል።
" ጉዳዩ #በህግ_አግባብ ተይዞ እየተጣራ ነው " ያለው ፓርቲው " በቀጣይ ሁኔታው የደረሰበት ደረጃ በሚመለከተው አካል ይገለፃል " ብሏል።
ፓርቲው በማእከላዊ ኮሚቴ አባሉ ላይ በደረሰው ህልፈት ሀዘን እንደተሰማው ገልጿል።
@tikvahethiopia
😢1.25K👍421🕊117😱67❤41🙏23👎22
TIKVAH-ETHIOPIA
ተጨማሪ መረጃዎች ፦ (ኢትዮ ቴሌኮም) #DevicePenetration 📱 በኢትዮጵያ 31 ሚሊየን (46%) ዜጎች የዘመናዊ ስልክ ( SmartPhone) ተጠቃሚዎች መሆናቸውን ኢትዮ ቴሌኮም አስታውቋል። ከዚህ ውጭ ያሉ (Basic Feature Phone) ተጠቃሚዎች ደግሞ 47.5 ሚሊዮን መድረሳቸውን ነው የተገለጸው። ዳታ የሚጠቀሙ መሳሪያዎች (Data Devices) ደግሞ 1.2 ሚሊዮን መድረሱን ገልጿል።…
" ከቀናት በፊት ኔትዎርክ ተቋርጦ የነበረው #በፋይበር ላይ በደረሰ ጉዳት ነው " - ኢትዮ ቴሌኮም
በበጀት ዓመቱ አጋማሽ ጉዳት የደረሰባቸው እንዲሁም የተጠገኑ የኔትወርክ ሳይቶች ስንት ናቸው ?
በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ኢትዮ ቴሌኮም በግጭት በግንባታ ሥራ፤ የዓለም አቀፍ መስመሮች መቋረጥና ብልሽት፤ በተፈጥሮ አደጋ እንዲሁም በኃይል መቆራረጥ ምክንያት ወደ 2,716 የሞባይል ኔትዎርክ ሳይቶቹ እንዲሁም 145 የመደበኛ ሳይቶቹ ሥራ ያቋረጡ መሆኑን ገልጿል።
እነዚህም በአብዛኛው በሰሜን እንዲሁም በምዕራብ የሀገሪቱ ክፍል የሚገኙ ናቸው። (🔴ከላይ በካርታው ተያይዟል)
በአንጻሩ በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት 413 የሞባይል ኔትወርክ ሳይቶች ጥገና ተደርጎላቸው ወደ አገልግሎት የገቡ ሲሆን ከፍተኛ ቁጥር የሚይዘው ጥገና በትግራይ ክልል በ174 ሳይቶች (28 ወረዳዎች/ከተማዎች) ወደ ላይ ተደርጎ ወደ አገልግሎት ተመልሰዋል።
በአጠቃላይ አገልግሎት በተቋረጠባቸው በ80 ወረዳዎችና ዋና ከተሞች የአገልግሎት ጥገና ተደርጎባቸዋል ተብሏል። [መሰረተ ልማቱን ለመጠገን የወጣው ወጪ እንዲሁም የደረሰው የጉዳት መጠን ከመግለጽ ተቆጥበዋል]
#FYI
- ኢትዮ ቴሌኮም፤ከሰሞኑ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ዳግም የኔትወርክ አገልግሎት ከጀመረ በኋላ ከቀናት በፊት የተቋረጠው #በፋይበር ላይ በደረሰ ጉዳት መሆኑን ገልጿል።
- በሰሜን ሪጅን (በአብዛኛው በትግራይ ክልል) ካሉ ከ700 በላይ ሰራተኞቹ ወደ 500 የሚጠጉት ዳግም ሥራ ለመጀመር አመልክተዋል ተብሏል።
- ከሰሞኑ በሰመራ የደረሰው የኔትወርክ መቆራረጥ በተወዳዳሪው [ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ] የመሰረተ ልማት ግንባታ መሆኑን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ የገለፁ ሲሆን በኩባንያው ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመጠየቅ ጉዳዩ #በህግ_ተይዟል ብለዋል።
@tikvahethiopia
በበጀት ዓመቱ አጋማሽ ጉዳት የደረሰባቸው እንዲሁም የተጠገኑ የኔትወርክ ሳይቶች ስንት ናቸው ?
በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት ኢትዮ ቴሌኮም በግጭት በግንባታ ሥራ፤ የዓለም አቀፍ መስመሮች መቋረጥና ብልሽት፤ በተፈጥሮ አደጋ እንዲሁም በኃይል መቆራረጥ ምክንያት ወደ 2,716 የሞባይል ኔትዎርክ ሳይቶቹ እንዲሁም 145 የመደበኛ ሳይቶቹ ሥራ ያቋረጡ መሆኑን ገልጿል።
እነዚህም በአብዛኛው በሰሜን እንዲሁም በምዕራብ የሀገሪቱ ክፍል የሚገኙ ናቸው። (🔴ከላይ በካርታው ተያይዟል)
በአንጻሩ በበጀት ዓመቱ ግማሽ ዓመት 413 የሞባይል ኔትወርክ ሳይቶች ጥገና ተደርጎላቸው ወደ አገልግሎት የገቡ ሲሆን ከፍተኛ ቁጥር የሚይዘው ጥገና በትግራይ ክልል በ174 ሳይቶች (28 ወረዳዎች/ከተማዎች) ወደ ላይ ተደርጎ ወደ አገልግሎት ተመልሰዋል።
በአጠቃላይ አገልግሎት በተቋረጠባቸው በ80 ወረዳዎችና ዋና ከተሞች የአገልግሎት ጥገና ተደርጎባቸዋል ተብሏል። [መሰረተ ልማቱን ለመጠገን የወጣው ወጪ እንዲሁም የደረሰው የጉዳት መጠን ከመግለጽ ተቆጥበዋል]
#FYI
- ኢትዮ ቴሌኮም፤ከሰሞኑ በሰሜኑ የሀገሪቱ ክፍል ዳግም የኔትወርክ አገልግሎት ከጀመረ በኋላ ከቀናት በፊት የተቋረጠው #በፋይበር ላይ በደረሰ ጉዳት መሆኑን ገልጿል።
- በሰሜን ሪጅን (በአብዛኛው በትግራይ ክልል) ካሉ ከ700 በላይ ሰራተኞቹ ወደ 500 የሚጠጉት ዳግም ሥራ ለመጀመር አመልክተዋል ተብሏል።
- ከሰሞኑ በሰመራ የደረሰው የኔትወርክ መቆራረጥ በተወዳዳሪው [ሳፋሪኮም ኢትዮጵያ] የመሰረተ ልማት ግንባታ መሆኑን የኢትዮ ቴሌኮም ዋና ስራ አስፈጻሚ የገለፁ ሲሆን በኩባንያው ላይ የደረሰውን ጉዳት ለመጠየቅ ጉዳዩ #በህግ_ተይዟል ብለዋል።
@tikvahethiopia
👍709👎95🕊21🙏20😢16❤15😱9🥰2🤔2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
" ... የቤተሰብ ዋነኛ ፍላጎት ፍትህን ማግኘትና እውነቱን ማወቅ ነው " - የአቶ በቴ ኡርጌሳ ቤተሰብ
የአቶ በቴ ኡርጌሳ ስርዓተ ቀብር ዛሬ ተፈፅሟል።
ስርዓተ ቀብራቸው ቤተሰቦቻቸው ፣ ዘመዶቻቸው በርካታ ሰዎች ፣ ወዳጆቻቸው በተገኙበት ዛሬ በመቂ መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው የተፈፀመው።
አንድ ቀላቸውን ለዶቼ ቨለ ሬድዮ የሰጡ የቤተሰብ አባል ፤ " ያው እንደ በቴ ከዚህ በላይ ብጠበቅም ብዙ ሰው ከሩቅም ከቅርብም መጥተው ስርዓተ ቀብራቸው ላይ ተገኝተው ቤተሰብም ቀብሩን ፈጽመው በሰላም ወደ ቤት ተመልሰዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
በትውልድ ከተማቸው መቂ ስርዓተ ቀብራቸው የተፈጸመው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ ማክሰኞ ሌሊት ተገድለው ትናንት ማለዳውን አስከሬናቸው ከመቂ ወደ ባቱ መውጫ መንገድ ላይ ተጥሎ መገኘቱ ይታወቃል።
የቤተሰቡ አባል ፤ " የበቴ አስክሬን ትናንት ጠዋት በአከባቢው ማህበረሰብ እና ቤተሰቦቻቸው ከመንገድ ተነስቶ ወደ ቤት ከተወሰደ በኋላ፤ ዛሬ ጠዋት ወደ አከባቢው ሆስፒታል በመውሰድ የአስከሬን ምርመራ ተደርጎለት ነበር፡፡ " ብለዋል።
" ቤተሰብ እንደ ትልቅ ነገር ያየው አንዴ የሞተውን ልጃቸውን ወስደው በስርዓቱ ቀብሩን መፈጸም ነው፡፡ ዛሬ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ አስከሬኑ እንዲመረመር የሆነው #በህግ_አዋቂዎች ምክር ነበር፡፡ ፖሊስ አስከሬኑን ወደ ምርመራ ባይወስድም ትናንት ጠዋት መረጃዎችን አሰባስቦ ሄዷል " ሲሉ ገልጸዋል።
እኚህ የቤተሰብ አባል በአቶ ቤተ አስከሬን የተለያዩ የሰውነት አካል ላይ በርካታ ያሉት ቦታ ላይ በጥይት ተደብድበው መገደላቸውን የሚያመላክት ብዙ ቁስሎች በአይናቸው መመልከታቸውን አስረድተዋል፡፡
" የቤተሰብ ዋነኛ ፍላጎት ፍትህን ማግኘት እና እውነቱን ማወቅ ነው " ብለዋል።
" ቤተሰብ የሆነው ነገር ምን እንደሆነ ማወቅ ይፈልጋል፡፡ በፍርድ ሂደት ፍትህ ቢገኝ ቤተሰቡንም የአከባቢውንም ማህበረሰብ የሚያረካ ጉዳይ ነው " ሲሉ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ተናግረዋል።
በግፍ ተገድለው አስክሬናቸው መንገድ ተጥሎ የተገኘው የኦነግ ከፍተኛ አመራር አቶ በቴ ኡርጌሳ ባለትዳርና የ4 ልጆች አባት ነበሩ።
@tikvahethiopia
የአቶ በቴ ኡርጌሳ ስርዓተ ቀብር ዛሬ ተፈፅሟል።
ስርዓተ ቀብራቸው ቤተሰቦቻቸው ፣ ዘመዶቻቸው በርካታ ሰዎች ፣ ወዳጆቻቸው በተገኙበት ዛሬ በመቂ መሰረተ ክርስቶስ ቤተክርስቲያን ነው የተፈፀመው።
አንድ ቀላቸውን ለዶቼ ቨለ ሬድዮ የሰጡ የቤተሰብ አባል ፤ " ያው እንደ በቴ ከዚህ በላይ ብጠበቅም ብዙ ሰው ከሩቅም ከቅርብም መጥተው ስርዓተ ቀብራቸው ላይ ተገኝተው ቤተሰብም ቀብሩን ፈጽመው በሰላም ወደ ቤት ተመልሰዋል " ሲሉ ተናግረዋል።
በትውልድ ከተማቸው መቂ ስርዓተ ቀብራቸው የተፈጸመው የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) የፖለቲካ ኦፊሰር አቶ በቴ ኡርጌሳ ማክሰኞ ሌሊት ተገድለው ትናንት ማለዳውን አስከሬናቸው ከመቂ ወደ ባቱ መውጫ መንገድ ላይ ተጥሎ መገኘቱ ይታወቃል።
የቤተሰቡ አባል ፤ " የበቴ አስክሬን ትናንት ጠዋት በአከባቢው ማህበረሰብ እና ቤተሰቦቻቸው ከመንገድ ተነስቶ ወደ ቤት ከተወሰደ በኋላ፤ ዛሬ ጠዋት ወደ አከባቢው ሆስፒታል በመውሰድ የአስከሬን ምርመራ ተደርጎለት ነበር፡፡ " ብለዋል።
" ቤተሰብ እንደ ትልቅ ነገር ያየው አንዴ የሞተውን ልጃቸውን ወስደው በስርዓቱ ቀብሩን መፈጸም ነው፡፡ ዛሬ ወደ ሆስፒታል ተወስዶ አስከሬኑ እንዲመረመር የሆነው #በህግ_አዋቂዎች ምክር ነበር፡፡ ፖሊስ አስከሬኑን ወደ ምርመራ ባይወስድም ትናንት ጠዋት መረጃዎችን አሰባስቦ ሄዷል " ሲሉ ገልጸዋል።
እኚህ የቤተሰብ አባል በአቶ ቤተ አስከሬን የተለያዩ የሰውነት አካል ላይ በርካታ ያሉት ቦታ ላይ በጥይት ተደብድበው መገደላቸውን የሚያመላክት ብዙ ቁስሎች በአይናቸው መመልከታቸውን አስረድተዋል፡፡
" የቤተሰብ ዋነኛ ፍላጎት ፍትህን ማግኘት እና እውነቱን ማወቅ ነው " ብለዋል።
" ቤተሰብ የሆነው ነገር ምን እንደሆነ ማወቅ ይፈልጋል፡፡ በፍርድ ሂደት ፍትህ ቢገኝ ቤተሰቡንም የአከባቢውንም ማህበረሰብ የሚያረካ ጉዳይ ነው " ሲሉ ለዶቼ ቨለ ሬድዮ ጣቢያ ተናግረዋል።
በግፍ ተገድለው አስክሬናቸው መንገድ ተጥሎ የተገኘው የኦነግ ከፍተኛ አመራር አቶ በቴ ኡርጌሳ ባለትዳርና የ4 ልጆች አባት ነበሩ።
@tikvahethiopia
😢665😭246❤155👏56🕊46😡30🙏23🤔17😱15🥰7