TIKVAH-ETHIOPIA
" ሁሉም ተፋላሚ ወገኖች የጦር ወንጀሎችን ፈፅመዋል " - አንቶኒ ብሊንከን አሜሪካ በትግራይ ተቀስቅሶ ወደ አማራ እና አፋር ክልሎች በተዛመተው ጦርነት ሁሉም ተፋላሚ ወገኖች የጦር ወንጀሎች ፈጽመዋል የሚል ድምዳሜ ላይ መድረሷን አሳውቃለች። ይህንን ያሳወቀችው ትላንት በውጭ ጉዳይ ቢሮዳ በኩል የአገራትን የሰብዓዊ መብቶች ይዞታን በተመለከተ የሚያደርገው ግምገማ ዓመታዊ ሪፖርት ይፋ ስታደርግ ነው። ሪፖርቱን…
#Update
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፦
• " የኢትዮጵያ መንግሥት በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መ/ቤት የቀረበበትን የሰብአዊ መብት ጥሰት ክስ በፍፁም አይቀበልም "
• " መግለጫው በሀገሪቱ አንድን ወገን በሌላኛው ላይ ለማነሣሣት ጥቅም ላይ ሊውል የሚችል ቆስቋሽ መግለጫ ነው "
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት " ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተከስቷል " ሲል የደረሰበትን ድምዳሜ የኢትዮጵያ መንግሥት በፍፁም እንደማይቀበለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቁን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ጉዳዩን በተመለከተ ያወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን እና የተመድ የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር በጋራ ካደረጉት ምርመራ አንፃር ሲታይ ምንም አዲስ ግኝት ያልተካተተበት ነው ብሏል።
በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግሥት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ያቀረበበትን ባዶ ውግዘት #በፍፁም እንደማይቀበለው ገልጿል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ያወጣው መግለጫ አንድን ወገን ብቻ መወንጀል ላይ ያነጣጠረ መሆኑንም ነው ሚኒስቴሩ የጠቆመው።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አማራጮችን ለመለየት ብሔራዊ ምክክር ለመጀመር በተዘጋጀችበት ወቅት ላይ የወጣ በመሆኑም መግለጫው ወቅቱን ያልጠበቀ ነው ብሎታል።
በተጨማሪም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ይህን መግለጫ ለማውጣት ያሰበበት ዓላማ ምንም ይሁን ምን መግለጫው በሀገሪቱ አንድን ወገን በሌላኛው ላይ ለማነሣሣት ጥቅም ላይ ሊውል የሚችል ቆስቋሽ መግለጫ ነው ሲል ገልጾታል።
@tikvahethiopia
የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ፦
• " የኢትዮጵያ መንግሥት በአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መ/ቤት የቀረበበትን የሰብአዊ መብት ጥሰት ክስ በፍፁም አይቀበልም "
• " መግለጫው በሀገሪቱ አንድን ወገን በሌላኛው ላይ ለማነሣሣት ጥቅም ላይ ሊውል የሚችል ቆስቋሽ መግለጫ ነው "
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት በሰሜን ኢትዮጵያ በተፈጠረው ጦርነት " ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት ተከስቷል " ሲል የደረሰበትን ድምዳሜ የኢትዮጵያ መንግሥት በፍፁም እንደማይቀበለው የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ማስታወቁን የኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘግቧል።
የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ጉዳዩን በተመለከተ ያወጣው መግለጫ የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብት ኮሚሽን እና የተመድ የሰብአዊ መብት ኮሚሽነር በጋራ ካደረጉት ምርመራ አንፃር ሲታይ ምንም አዲስ ግኝት ያልተካተተበት ነው ብሏል።
በመሆኑም የኢትዮጵያ መንግሥት ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ያቀረበበትን ባዶ ውግዘት #በፍፁም እንደማይቀበለው ገልጿል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ያወጣው መግለጫ አንድን ወገን ብቻ መወንጀል ላይ ያነጣጠረ መሆኑንም ነው ሚኒስቴሩ የጠቆመው።
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ የሽግግር ፍትሕ ፖሊሲ አማራጮችን ለመለየት ብሔራዊ ምክክር ለመጀመር በተዘጋጀችበት ወቅት ላይ የወጣ በመሆኑም መግለጫው ወቅቱን ያልጠበቀ ነው ብሎታል።
በተጨማሪም የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ መሥሪያ ቤት ይህን መግለጫ ለማውጣት ያሰበበት ዓላማ ምንም ይሁን ምን መግለጫው በሀገሪቱ አንድን ወገን በሌላኛው ላይ ለማነሣሣት ጥቅም ላይ ሊውል የሚችል ቆስቋሽ መግለጫ ነው ሲል ገልጾታል።
@tikvahethiopia
👎1.21K👍757❤72🕊35🤔18😱17😢7🥰6🙏2