TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
#የእሳት_አደጋ_በሀዲያ_ዞን

በሀዲያ ዞን ምሻ ወረዳ በሶስት ቀበሌዎች ፦
- ኤራ ጌሜዶ፣
- ኩናፋ
- ጉና ሜጋቾ በደረሰ እሳት አደጋ 4 መቶ 36 የቤተሰብ አባላት መፈናቀላቸውን የዞኑ የአደጋ ስጋት ሥራ አመራር ጽ/ቤት አሳውቋል።

ፅህፈት ቤቱ አደጋው የተፈጥሮ እሳት አደጋ ነው ብሏል።

በደረሰው አደጋ ከ23 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መዉደሙ ተጠቁሟል፡፡

በአደጋው በሰው ህይወት ላይ የደረሰ ጉዳት የለም።

128 ዶሮዎች፣ 243 ኩንታል የተለያዩ የእህል ዘሮች ፣ 18 የንብ ቀፎዎች፣ የተለያዩ የቤት ቁሳቁሶች እና በአካባቢው የነበሩ የጓሮ አትክልቶች በድምሩ ከ23 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሟል።

በሌላ መረጃ ፦

በምዕራብ ሶሮ ወረዳ በጃቾ ከተማ በደረሰ የእሳት አደጋ ከ250 ሺህ ብር በላይ የሚገመት ንብረት ወድሟል።

አደጋው ታህሳስ 18 ከምሽቱ 2፡30 በመብራት ኮንታክት የደረሰ መሆኑን የወረደው ፖሊስ ጽ/ቤት አስታውቋል።

አደጋው ህብረተሰቡና የፖሊስ አካላት ባደረጉት ርብርብ ወደ ሌሎች ሱቆችና መኖርያ ቤቶች ሳይሻገር በቁጥጥር ስር መዋሉን ተገልጿል።

(ሀዲያ ዞን ኮሚኒኬሽን)
@tikvahethiopiaBOT @tikvahethiopia
#የእሳት_አደጋ

ከየካቲት ወር መጀመሪያ እስከአሁን የተከሰቱ የእሳት አደጋዎች፦

#AddisAbaba📍

- በንፋስ ስልክ ክፍለ ከተማ ወረዳ አምስት ሂርቱ ሞጆ ተብሎ በሚጠራው የጥብቅ ደን ውስጥ ለቆሻሻ ተብሎ የተለኮሰ እሳት ባስከተለው አደጋ 200 ሺህ ብር የሚደርስ ንብረት ሙሉ በሙሉ ወድሟል።

- በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 01 ጎማ ተራ አካባቢ በሚገኝ አንድ አነስተኛ ሆቴል በተከሰተ አደጋ 300 ሺህ ብር የሚጠጋ ንብረት መውድሟል።

- በጉለሌ ክፍለ ከተማ በእፅዋት ማእከል በተነሳ የሰደድ እሳት 10ሺህ ብር የሚደርስ ንብረት ለውድመት ተዳርጓል።

- በአዲስ አበባ አዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 ልዩ ቦታ ኮልፌ እፎይታ ገበያ ማዕከል ፊትለፊት በአራት የንግድ ሱቆቸ በሆኑ የጫማ ማምረቻ እና መሸጫ እንዲሁም ጨርቃ ጨርቅ መሸጫ ላይ በደረሰ ድገተኛ የእሳት አደጋ ሰባት ሚሊዮን ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል።

- በአዲስ አበባ ከተማ ቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አንድ ልዩ ስሙ ቦሌ ሚካኤል በተባለ አከባቢ በዶልፊን ኢትዮጲያ የሳሙናና ሻምፖ ማምረቻ ፋብሪካ ላይ በደረሰ የእሳት አደጋ የ1 ሚሊዮን 85 ሺህ ብር የሚገመት ንብረት ወድሟል።

- በአዲስ ከ/ክፍለ ከተማ ወረዳ 4 መሳለሚያ አከባቢ አራት የንግድ ሱቆች ላይ እና ወረዳ 1 መርካቶ አከባቢ 3 ንግድ ሱቆች በተጨማሪም የካ ክ/ከተማ ወረዳ 8 ዘፍነሽ ህንፃ አከባቢ በሶስት ንግድ ሱቆች ላይ በደረሱ የእሳት አደጋዎች ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ንብረት ወደመ።

- በአዲስ አበባ በቦሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ 14 ገረጂ ኖክ ማደያ 40/60 ኮንዶሚኒየም 13ኛ ፎቅ ላይ ለኮንስትራክሽን ግብዓት የሚውሉ በደረሰ የእሳት አደጋ የ200 ሺህ ብር ንብረት ወድሟል።

ይቀጥላል👇
👍256😢49😱10👎7👏7🥰1