TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
62.9K photos
1.61K videos
216 files
4.37K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
"...ወታደሮቼ በሰሜን ኢትዮጵያ ግጭት አልተሳተፉም" - ሶማሊያ

የሶማሊያ መንግሥት ወታደሮቹ በሰሜን ኢትዮጵያው ግጭት ተሳትፈዋል ሲሉ የወጡ ዘገባዎች ትክክል አይደሉም አለ።

ይህን ያለው የቀድሞ የሶማሊያ ከፍተኛ የደኅንነት ባለስልጣን ከጥቂት ወራት በፊት ኤርትራ ውስጥ ወታደራዊ ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ በመቶዎች የሚቆጠሩ የሶማሊያ ወታደሮች ኢትዮጵያ ውስጥ ተገድለዋል ካሉ በኋላ ነው።

አብዲሰላም ጉሌድ የተባሉት የሶማሊያ ብሔራዊ የደኅንነትና መረጃ ተቋም የቀድሞ ምክትል ኃላፊ ተጨባጭ #ማስረጃ ሳያቀርቡ ለአንድ የግል ሬዲዮ "400 የሚደርሱ የሶማሊያ ወታደሮች" በትግራይ ክልል በተካሄደው ውጊያ ተገድለዋል ሲሉ ተናግረዋል።

የቀድሞው ባለስልጣን ከኢትዮጵያ የመከላከያ ሠራዊት ጋር ተሰልፈው ሲዋጉ ተገድለዋል ያሏቸው የሶማሊያ ወታደሮች በ20 እና በ30 ዓመት ዕድሜ ውስጥ የነበሩ ናቸው።

ይህ የግለሰቡ ንግግር በተለያዩ የሶማሊያ ክፍሎች ውስጥ ቁጣን ቀስቅሷል።

ልጆቻቸው ለወታደራዊ ስልጠና ወደ ውጪ አገራት የሄዱ ቤተሰቦች ጉዳዩ እንዳሳሰባቸው በመግለጽ መንግሥት ልጆቻቸው የት እንዳሉ እና በሕይወት ይኑሩ ወይም ይሙቱ ማብራሪያ እንዲሰጥ ጠይቀዋል።

የሶማሊያው የማስታወቂያ ሚኒስትር ኦስማን አቡከር ዱቤ ፥ "የሶማሊያ ኃይሎች በቅርቡ በኢትዮጵያ በተካሄደው ውጊያ ላይ አልተሳተፉም" ብለዋል።

ሚኒስትሩ ከቢቢሲ የሶማሊኛ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልልስ "ከዚህ ቀደም የሶማሊያ ወታደሮች በሊቢያና በአዘርባጃን ውስጥ በተካሄዱ ውጊያዎች ውስጥ ተሳትፈዋል ተብሎ ቢወራም ኋላ ወሬው ሐሰተኛ መሆኑ ተረጋግጧል" ብለዋል።

ጨምረው የሶማሊያ ወታደሮች በኢትዮጵያው ግጭት ውስጥ ተሳትፈዋል የተባለው ወሬ ሐሰተኛ ነው ብለዋል። ~ ቢቢሲ

@tikvahethiopiaBot @tikvahethiopia
የ12ኛ ክፍል ፈተና ጉዳይ !

የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና መሰጠት ከጀመረ ዛሬ 3ኛ ቀኑን ይዟል። ፈተናው በነገው ዕለት ይጠናቀቃል።

ፈተናው መሰጠት በጀመረበት ሰኞ ኅዳር 29/2024 ዓ.ም ፈተናው ተሰርቋል የሚሉ ወሬዎች ቢናፈሱም፤ ፈተናው አለመሰረቁን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ አሳውቀው እንደነበር አይዘነጋም።

"ተማሪዎች ተረጋግተው ይፈተኑ" በሚል ይመስላል መንግስት የማህበራዊ ሚዲያዎችን ቢያግዳቸውም የተለያዩ ዘዴዎችን በመጠቀም ከፈተና ክፍል ውስጥ የተነሱ ፎቶዎች ባለፉት 2 ቀናት በቴሌግራም ግሩፖች ላይ ሲዘዋወሩ ታይተዋል።

ትላንት ለሊት አንስቶ ግን ዛሬ የተሰጡት (የባዮሎጂ፣ ታሪክና ኬሚስትሪ) ፈተናዎች ቀድመው በማህበራዊ ሚዲያ ላይ መውጣታቸውን ቲክቫህ ኢትዮጵያ ለማረጋገጥ ችሏል።

ቲክቫህ ኢትዮጵያ ከፈተናው ጋር በተያያዘ በርካታ የቤተሰቡ አባላት የሰጡትን ጥቆማ እና ትላንት የተለያዩ ግሩፖች ላይ የተለጠፉትን የፈተና ወረቀቶች (በPDF እንዲሁም በፎቶ) በመያዝ ዛሬ ከፈተናው በኃላ ባደረገው ማጣራት ፈተናዎቹ እራሳቸው ሆኖ አግኝቷቸዋል።

ከበቂ #ማስረጃ ጋር ለማረጋገጥ የቻልነው የዛሬው ፈተና ለተፈታኞች ከመሰጠቱ ከሰዓታት በፊት ቀደም ብሎ በማህበራዊ ሚዲያ ላይ መውጣቱን ነው።

ቴሌግራምን ጨምሮ ማኅበራዊ ትስስር ገፅ ፈተናው ከጀመረ ቀን ጀምሮ ቢቋረጥም በቀላሉ በ VPN ግንኙነቱን ማስቀጠል በመቻሉ ተማሪዎች ሲቀባበሉት አስተውለናል።

ለዓመታት የደከሙ ተማሪዎችን ልፋት ከንቱ በሚያስቀርና ትውልድን በሚገድል ድርጊት የተሳተፉ፣ የሚተባበሩ፣ የሚያጋሩ አካላት ከዚህ ድርጊታቸው ሊታቀቡ ይገባል።

መንግስት ይህንን ፈትሾ ተጠያቂ መሆን ያለበትን አካል በአፋጣኝ ማሳወቅ ይኖረበታል ሲሉ የቲክቫህ ቤተሰብ የሆኑ ተማሪዎችና የተማሪ ወላጆች ጥሪ አቅርበዋል።

@tikvahethiopia
👍2
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#እንድታውቁት

በአዲስ አበባ ታግዶ የቆየው የነዋሪነት መታወቂያ #የጠፋባቸው ነዋሪዎች ምትክ አገልግሎት ከፊታችን ሰኞ ይጀምራል።

የአዲስ አበባ ወሳኝ ኩነት ምዝገባና መረጃ ኤጀንሲ አገልግሎቱ ከሰኞ ታህሳስ 24 ጀምሮ ለመጀመር ዝግጅት እንዳጠናቀቀ አረጋግጧል።

ኤጀንሲው ፤ በቀድሞ አሰራር ፖሊስ ግለሰቦች በነዋሪነት የተመዝገቡ ነዋሪ መሆናቸው በተቋሙ ሳይረጋገጥ የጠፋ ሰነዶችን ማስረጃ ሲሰጥበት የነበረበት አሰራር ግለሰቦች በሃሰተኛ የእምነት ቃል የነዋሪነት መታወቂያ ሳይኖራቸው ማስረጃውን በማውጣት በተለያዩ ቦታዎች ማስረጃውን እየጠተቀሙ እያጭበረበሩ መሆኑን የፖሊስ ምርመራ በተለያዩ ግዝያት ማረጋገጡን ገልጿል።

አሁን ካለው  ጥብቅ የነዋሪነት መታወቂያ  አሰጣጥ ቁጥጥር ስርዓት አንፃር ማንኛውም የጠፋበት ምትክ ጠያቂ  ነዋሪዎች ቀድሞ ነዋሪ መሆናቸውን ከሚኖሩበት የወረዳ ጽ/ቤቶች ማረጋገጫ ለፖሊስ ሲያቀረቡና ከፖሊስ የጠፋ ሰነድ #ማስረጃ_ሲሰጣቸው _ብቻ አገልግሎቱን እንደሚያገኙ ማሳሰቢያ ተሰጥቷል።

ኤጀንሲው ፤ የጤና እክል ያለባቸው እንዲሁም ለአቅመ ደካሞች ልዩ ድጋፍ እንደሚያደርግ አሳውቋል።

@tikvahethiopia
👍926👎110🙏38😢3718😱16🕊16🥰9