TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.62K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Grade12NationalExam

ከዚህ ቀደም በ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ላይ ሲሰጡ ከነበሩ የትምህርት አይነቶች መካከል ሥነ ምግባርና የሥነ ዜጋ ትምህርት (Civics and Ethical Education) በዘንድሮው ዓመት 2016 ዓ/ም #አይሰጥም

የሥነምግባር እና ሥነ ዜጋ ትምህርት (Civics and Ethical Education) ፈተና ያልተካተተው በሁለቱም የተፈጥሮ ሳይንስ እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ የትምህርት ዘርፎች ነው።

ይህ ፈተና ለምን በብሄራዊ ፈተናው ላይ እንዳልተካከተተ / እንዳይካተት ውሳኔ እንደተለለፈ ትምህርት ሚኒስቴር የሰጠው ዝርዝር ማብራሪያ የለም።

በሌላ በኩል ፤ ባለፉት ዓመታት ለማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ሳይሰጥ የቆየው #የኢኮኖሚክስ ትምህርት በዚህ ዓመት 2016 ፈተና ላይ ተካቷል።

በዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ፈተና የተፈጥሮ ሳይንስ እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች እኩል ስድስት ትምህርቶችን ይወስዳሉ።

የተፈጥሮ ሳይንስ ፤ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ ፣ ፊዚክስ ፣ ኬሚስትሪ፣ ባዮሎጂ፣ ሶኮላስቲክ አፕቲቲውድ ቴስት ፈተና ሲወስዱ የማህበራዊ ሳይንስ ደግሞ እንግሊዝኛ፣ ሒሳብ፣ ታሪክ ፣ ጂኦግራፊ ፣ ኢኮኖሚክስ እና ስኮላስቲክ አፕቲቲውድ ፈተና የሚወስዱ ይሆናል።

በዚሁ ዝርዝር መሰረት ከሁለቱም ዘርፎች የሥነ ዜጋና ሥነምግባር (Civics and Ethical Education) ትምህርት የወጣ ሲሆን የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና ላይ ባለፉት ዓመታት ሳይሰጥ የቀረው ኢኮኖሚክስ ተካቷል።

ፈተናው የሚሰጥበት ትክክለኛውና ቁርጥ ያለው ቀን ባይታወቅም እንደ ከዚህ ቀደሞቹ ዓመታት ተማሪዎችን ወደ ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት (#ዩኒቨርሲቲዎች) በማስገባት እንደሚሰጥ ይጠበቃል።

@tikvahethiopia
😭808266😡134🙏112🕊53🥰45😱38😢30
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#ሲቢኢ #ዩኒቨርሲቲዎች #ኦዲት

" ባንኩ ላይ የሳይበር ጥቃት ደርሷል፤ ዝውውሩም አይታወቅም ብለው አስበው ነው ያደረጉት " - አቶ አቤ ሳኖ

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዜዳንት አቶ አቤ ሳኖ በዩኒቨርሲቲዎች አካባቢ ስለነበረው የመጋቢት 6 ለሊት የገንዘብ ዝውውር እና አጠቃላይ ወጭ ስለተደረገው / አሁን ስለተመለሰው የገንዘብ መጠን ምን አሉ ?

አቶ አቤ ሳኖ ፦

" የተቋረጠውን አገልግሎት ካስጀመርን በኃላ ወደ ግብይቶች ምርመራ ነው የገባነው።

በዛ ያለ ግብይት ያደረጉትን ለይተናቸው የፍትሕ አካላት እንዲያውቁት አድርገናል። በብዛት በዛ ያለ ቁጥር ያለው እጅግ በጣም በሚያሳዝን ሁኔታ #በዩኒቨርሲቲዎች አካባቢ ነው።

ተማሪዎቹ (የዩኒቨርሲቲ ማህበረሰብ) ያሰቡት ባንኩ ላይ የሳይበር ጥቃት ደርሷል ብለው ነው። ስለዚህ የሚደረገው ግብይት (ወጭ / ዝውውር) አይታወቅም ብለው ነው ያደረጉት።

አሁን ላይ ግን ግብይቱ እንደሚታወቅ ሲያውቁ የወሰዱትን ገንዘብ እየመለሱ ነው ያሉት። አሁንም እንዲመልሱ ነው የምንፈልገው።

የወሰዱትን ገንዘብ ከመለሱ ወደ ክስ አንሄድም። የማይመልሱ ከሆነ ግን የህግ እርምጃ እንወስዳለን።

ዝርዝር ጉዳዩ (ከገንዘብ ዝውውር/ወጭ የተደረገ/የተመለሰ) ኦዲት ተደርጎ ሲያልቅ ይቀርባል።

የኦዲት ሂደቱ ስላላለቀ በዚህ መካከል ሌሎች ነገሮችን ማንሳት ከፋይናንሻል ኦዲት አካሄድ ጋር የሚሄድ ስላልሆነ አንዳንድ የህጋዊ እርምጃዎችም ሊከተሉ ስለሚችሉ ጥንቃቄ ስለሚፈልግ ነው። "

@tikvahethiopia
🤔982327😡222😭129👏96🕊61🙏51🥰40😢40😱28