TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.38K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

በቱርክ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ 99.38 በመቶ ድምፅ የተቆጠረ ሲሆን እስካሁን ድረስ ከ50 በመቶ በላይ ድምፅ ያገኘ እንደሌለ የሚወጡት ሪፖርቶች አሳይተዋል።

በምርጫው ትልቅ ግመት የተሰጣቸው ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ፤ 49.42 ድምፅ ያገኙ ሲሆን ተቀናቃኛቸው ከማል ኪሊዳሮግሉ 44.95 ድምፅ አገኝተዋል።

በሌላ በኩል ትላንት ምሽት ፕሬዜዳንት ኤርዶጋን በፓርቲያቸው ፅ/ቤት ለደጋፊዎቻቸው ንግግር አድርገው ነበር።

ምን አሉ ?

- የመጀመሪያ ደረጃ ውጤቶች በሰፊ ልዩነት እየመራን መሆኑን ያሳያሉ።

- የሀገር ውስጥ እንዲሁም የውጭ ድምፅ ቆጠራው ይቀጥላል። (በቱርክ ምርጫ በውጭ ያሉ የቱርክ ዜጎችም ድምፅ የሚሰጡበት መንገድ ያለ ሲሆን በአሁንም ምርጫ ድምፃቸውን ሰጥተዋል)

- እነሱ (ተቃዋሚዎች) " እየመራን ነው " እያሉ ሰዎችን ለማሞኘት እየሞከሩ ነው።

- ፕሬዜዳንታዊ ምርጫው በመጀመሪያው ዙር ይጠናቀቅ እንደሆነ እስካሁን #አናውቅም

- ከእኛ የቅርብ ተቀናቃኝ በ2.6M ድምጽ ርቀናል።

- በመጀመሪያው ዙር እንደምናሸንፍ እናምናለን።

- በታሪካችን ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምርጫ ነበር የተሳተፈው።

በቱርክ ምርጫ ላይ አንድ ተወዳደሪ ለማሸነፍ በመጀመሪያ ዙር ከ50 በመቶ በላይ ድምጽ ያስፈልገዋል።

ተወዳዳሪዎች 50 በመቶውን ድምፅ ማለፍ ካልቻሉ ፤ ከሁለት ሳምንት በኋላ በሁለተኛ ዙር ምርጫ ይገናኛሉ።

አሁን ባለው ሁኔታ ምርጫው ወደ ሁለተኛ ዙር የማምራቱ እድል ሰፊ መሆኑ ተነግሯል።

መረጃው የአናዱሉ እና የቲአርቲ ወርልድ ነው።

@tikvahethiopia
👍729103👎24🙏18😢11😱9🕊7🥰6