TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
በቱርክ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ 99.38 በመቶ ድምፅ የተቆጠረ ሲሆን እስካሁን ድረስ ከ50 በመቶ በላይ ድምፅ ያገኘ እንደሌለ የሚወጡት ሪፖርቶች አሳይተዋል።
በምርጫው ትልቅ ግመት የተሰጣቸው ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ፤ 49.42 ድምፅ ያገኙ ሲሆን ተቀናቃኛቸው ከማል ኪሊዳሮግሉ 44.95 ድምፅ አገኝተዋል።
በሌላ በኩል ትላንት ምሽት ፕሬዜዳንት ኤርዶጋን በፓርቲያቸው ፅ/ቤት ለደጋፊዎቻቸው ንግግር አድርገው ነበር።
ምን አሉ ?
- የመጀመሪያ ደረጃ ውጤቶች በሰፊ ልዩነት እየመራን መሆኑን ያሳያሉ።
- የሀገር ውስጥ እንዲሁም የውጭ ድምፅ ቆጠራው ይቀጥላል። (በቱርክ ምርጫ በውጭ ያሉ የቱርክ ዜጎችም ድምፅ የሚሰጡበት መንገድ ያለ ሲሆን በአሁንም ምርጫ ድምፃቸውን ሰጥተዋል)
- እነሱ (ተቃዋሚዎች) " እየመራን ነው " እያሉ ሰዎችን ለማሞኘት እየሞከሩ ነው።
- ፕሬዜዳንታዊ ምርጫው በመጀመሪያው ዙር ይጠናቀቅ እንደሆነ እስካሁን #አናውቅም።
- ከእኛ የቅርብ ተቀናቃኝ በ2.6M ድምጽ ርቀናል።
- በመጀመሪያው ዙር እንደምናሸንፍ እናምናለን።
- በታሪካችን ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምርጫ ነበር የተሳተፈው።
በቱርክ ምርጫ ላይ አንድ ተወዳደሪ ለማሸነፍ በመጀመሪያ ዙር ከ50 በመቶ በላይ ድምጽ ያስፈልገዋል።
ተወዳዳሪዎች 50 በመቶውን ድምፅ ማለፍ ካልቻሉ ፤ ከሁለት ሳምንት በኋላ በሁለተኛ ዙር ምርጫ ይገናኛሉ።
አሁን ባለው ሁኔታ ምርጫው ወደ ሁለተኛ ዙር የማምራቱ እድል ሰፊ መሆኑ ተነግሯል።
መረጃው የአናዱሉ እና የቲአርቲ ወርልድ ነው።
@tikvahethiopia
በቱርክ ፕሬዝዳንታዊ ምርጫ 99.38 በመቶ ድምፅ የተቆጠረ ሲሆን እስካሁን ድረስ ከ50 በመቶ በላይ ድምፅ ያገኘ እንደሌለ የሚወጡት ሪፖርቶች አሳይተዋል።
በምርጫው ትልቅ ግመት የተሰጣቸው ፕሬዝዳንት ኤርዶጋን ፤ 49.42 ድምፅ ያገኙ ሲሆን ተቀናቃኛቸው ከማል ኪሊዳሮግሉ 44.95 ድምፅ አገኝተዋል።
በሌላ በኩል ትላንት ምሽት ፕሬዜዳንት ኤርዶጋን በፓርቲያቸው ፅ/ቤት ለደጋፊዎቻቸው ንግግር አድርገው ነበር።
ምን አሉ ?
- የመጀመሪያ ደረጃ ውጤቶች በሰፊ ልዩነት እየመራን መሆኑን ያሳያሉ።
- የሀገር ውስጥ እንዲሁም የውጭ ድምፅ ቆጠራው ይቀጥላል። (በቱርክ ምርጫ በውጭ ያሉ የቱርክ ዜጎችም ድምፅ የሚሰጡበት መንገድ ያለ ሲሆን በአሁንም ምርጫ ድምፃቸውን ሰጥተዋል)
- እነሱ (ተቃዋሚዎች) " እየመራን ነው " እያሉ ሰዎችን ለማሞኘት እየሞከሩ ነው።
- ፕሬዜዳንታዊ ምርጫው በመጀመሪያው ዙር ይጠናቀቅ እንደሆነ እስካሁን #አናውቅም።
- ከእኛ የቅርብ ተቀናቃኝ በ2.6M ድምጽ ርቀናል።
- በመጀመሪያው ዙር እንደምናሸንፍ እናምናለን።
- በታሪካችን ከፍተኛ ቁጥር ያለው ምርጫ ነበር የተሳተፈው።
በቱርክ ምርጫ ላይ አንድ ተወዳደሪ ለማሸነፍ በመጀመሪያ ዙር ከ50 በመቶ በላይ ድምጽ ያስፈልገዋል።
ተወዳዳሪዎች 50 በመቶውን ድምፅ ማለፍ ካልቻሉ ፤ ከሁለት ሳምንት በኋላ በሁለተኛ ዙር ምርጫ ይገናኛሉ።
አሁን ባለው ሁኔታ ምርጫው ወደ ሁለተኛ ዙር የማምራቱ እድል ሰፊ መሆኑ ተነግሯል።
መረጃው የአናዱሉ እና የቲአርቲ ወርልድ ነው።
@tikvahethiopia
👍729❤103👎24🙏18😢11😱9🕊7🥰6