TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update
ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ጉዳይ መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና ጅቡቲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ሕክምናቸውን አጠናቀው ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም ወደ ሀገራቸው እንደሚመለሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር አስታውቋል።
ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ክሊቭላንድ ክሊኒክ ሆስፒታል አቡዳቢ (Cleveland Clinic Abu Dhabi) በቅዱስ ሲኖዶስ እና በጠቅላይ ቤተክህነት ፈቃድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር አስፈላጊውን የዝውውር ሂደት ከባለሙያዎች ጋር በማመቻቸት ግንቦት 3 ቀን 2014 ዓ.ም መጓዛቸውና ሕክምናቸውን በዚያው ሲከታተሉ ቆይተዋል።
ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ጤንነታቸው በአሁኑ ሰዓት #በመልካም ሁኔታ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሕክምናቸውን በማጠናቀቅ ወደ ኢትዮጵያ ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም ላይ ከማኅበሩ የሕክምና ቡድን ጋር ይመለሳሉ መባሉን ከEOTC ያገኘነው መረጃ ያመልክታል።
@tikvahethiopia
ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ጉዳይ መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና ጅቡቲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ሕክምናቸውን አጠናቀው ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም ወደ ሀገራቸው እንደሚመለሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር አስታውቋል።
ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ክሊቭላንድ ክሊኒክ ሆስፒታል አቡዳቢ (Cleveland Clinic Abu Dhabi) በቅዱስ ሲኖዶስ እና በጠቅላይ ቤተክህነት ፈቃድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር አስፈላጊውን የዝውውር ሂደት ከባለሙያዎች ጋር በማመቻቸት ግንቦት 3 ቀን 2014 ዓ.ም መጓዛቸውና ሕክምናቸውን በዚያው ሲከታተሉ ቆይተዋል።
ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ጤንነታቸው በአሁኑ ሰዓት #በመልካም ሁኔታ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሕክምናቸውን በማጠናቀቅ ወደ ኢትዮጵያ ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም ላይ ከማኅበሩ የሕክምና ቡድን ጋር ይመለሳሉ መባሉን ከEOTC ያገኘነው መረጃ ያመልክታል።
@tikvahethiopia
👍10❤1🙏1