TIKVAH-ETHIOPIA
1.53M subscribers
63.1K photos
1.61K videos
217 files
4.39K links
ይህ የቲክቫህ (ተስፋ) ኢትዮጵያ ቤተሰብ አባላት መሰባሰቢያ እንዲሁም የመረጃ እና የመልዕክት መለዋወጫ መድረክ ነው።

መረጃ እና መልዕክት ፦ 0919743630

ማርኬቲንግ ፦ 0979222111 ወይም
0979333111

@tikvahuniversity
@tikvahethAfaanOromoo
@tikvahethmagazine
@tikvahethsport
@tikvahethiopiatigrigna

#ኢትዮጵያ
Download Telegram
TIKVAH-ETHIOPIA
Photo
#Update

ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽ/ቤትና የውጭ ጉዳይ መምሪያ የበላይ ኃላፊ የድሬዳዋና ጅቡቲ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስና የቅዱስ ሲኖዶስ አባል ሕክምናቸውን አጠናቀው ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም ወደ ሀገራቸው እንደሚመለሱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር አስታውቋል።

ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ለከፍተኛ ሕክምና ወደ ክሊቭላንድ ክሊኒክ ሆስፒታል አቡዳቢ (Cleveland Clinic Abu Dhabi) በቅዱስ ሲኖዶስ እና በጠቅላይ ቤተክህነት ፈቃድ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ሕክምና ማኅበር አስፈላጊውን የዝውውር ሂደት ከባለሙያዎች ጋር በማመቻቸት ግንቦት 3 ቀን 2014 ዓ.ም መጓዛቸውና ሕክምናቸውን በዚያው ሲከታተሉ ቆይተዋል።

ብፁዕ አቡነ አረጋዊ (ዶ/ር) ጤንነታቸው በአሁኑ ሰዓት #በመልካም ሁኔታ ላይ የሚገኝ ሲሆን ሕክምናቸውን በማጠናቀቅ ወደ ኢትዮጵያ ሐምሌ 8 ቀን 2014 ዓ.ም ላይ ከማኅበሩ የሕክምና ቡድን ጋር ይመለሳሉ መባሉን ከEOTC ያገኘነው መረጃ ያመልክታል።

@tikvahethiopia
👍101🙏1